top of page

ግንቦት 12 2017 የከተማ መሬት ይዞታና የመሬት ነክ ንብረት ምዝገባ ረቂቅ አዋጅ ፀደቀ

  • sheger1021fm
  • May 20
  • 1 min read

የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት አካሂዷል።


በዚህም ምክር ቤቱ በከተማ መሰረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቀረበለት የከተማ መሬት ይዞታና የመሬት ነክ ንብረት ምዝገባ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ፤ የከተማ መሬት ይዞታና የመሬት ነክ ንብረት ምዝገባ ረቂቅ አዋጅን በ2 ተቃውሞ በ3 ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።


አዋጁ የከተማ መሬት አያያዝ ወጥነት ባለው መልኩ በማደራጀት በመላው የሃገሪቱ ከተሞች ያሉ የመሬት ይዞታዎችን መመዝገብ አስፈላጊ በመሆኑ የተሰናዳ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡


በመሆኑ ወደ ተግባር ሲገባ የመሬት አስተዳደር ስርዓትን ያቀለጥፋል፤ ህገ ወጥ የመሬት ወረራን፤ ብልሹ አሰራርንና ኢ-ፍትሃዊነትን ለማስቀረት ይረዳል ተብሎም ታምኖበታል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…






Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page