ግብርናው ዘርፍ የብድር አቅርቦት ከማያገኙ ዘርፎች መካከል ቀዳሚው ነው ተባለ፡፡
- sheger1021fm
- 8 minutes ago
- 1 min read
ታህሳስ 21/2018
ግብርናው ዘርፍ የብድር አቅርቦት ከማያገኙ ዘርፎች መካከል ቀዳሚው ነው ተባለ፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ግብርናው የብድር አቅርቦት ከፋይናንስ ተቋማት እንዳያገኝ ከሚያደርጉት ምክንያቶች ዋነኛው በዝናብ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ነው ይላሉ ያነጋገርናቸው የግብርና ኦኮኖሚ ባለሙያ፡፡
በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የግብርና ኢኮኖሚስት ምርምር ዳይሬክተር እና ተመራማሪ ታደለ ማሞ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚቀርበው ብድር ውስጥ ግብርናው የሚያገኘው 10 በመቶ ብቻ ነው፡፡
ከ10 በመቶ ብድሩ መካከል አብዛኛው ብድር በግብርና ምርት ማቀነባበር ስራ ለተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች የሚቀርብ ነው ተብሏል፡፡ ገበሬው አሁንም ብድር እያገኘ አይደለም ብለዋል፡፡
ግብርናው ለሺህ አመታት በስፋት የሚያውቀው ቴክኖሎጂ በሬና ሞፈር ነው ፣ ገበሬውም የለመደው ዝናብን ጠብቆ ማምረት ነው ይህ ደግሞ ለፋይናንስ ተቋማቱ ለዘርፉ ብድር ለመስጠት የሚያስችላቸው አይደለም ሲሉ ጠቅሰዋል፡፡

ከተሞች አካባቢ የግብርና ምርት አንድ ሰሞን ዋጋው ሲንር ሌላ ጊዜ ደግሞ የምርቱ ዋጋ ዝቅ ሲል ይታያል ይህ የሚሆነው ገበሬው በአግባቡ የብድር አቅርቦት ስለማያገኝ ነው ብለዋል ዶክተር ታደለ ማሞ፡፡
እንዳመረተ ገበሬው ሕይወቱን የሚመራበትና የተሻለ ስራ ለመስራት የሚያስችለው ፋይናንስ ይፈልጋል ይህ ደግሞ በወቅቱ ስለማያገኝ ያመረተውን ምርት ባገኘው ዋጋ ለመሸጥ ይገደዳል ይላሉ፡፡
ይህም የግብርና ምርቶች ወቅታዊ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል ሲሉም አስረድተዋል፡፡
ግብርናው እንዲዘምንና የገበሬው ሕይወት ለመለወጥ ምርቶች ከአመት እስከአመት ወጥ በሆነ መንገድ ለማቅረብ ከተፈለገ የመስኖ ግብርና ማስፋፋት ፣ ግብርና ለማዘመን በማሰብ ይቋቋማል የተባለው የግብርና ባንክ ማቋቋምና ወደ ስራ ማስገባት ይገባል ብለዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1








