ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (IGAD) የህይወት ዘመን ጋዜጠኝነት ሽልማት ተሰጣቸው።
- sheger1021fm
- 6 hours ago
- 1 min read
ህዳር 22 2018
ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን (IGAD) የህይወት ዘመን ጋዜጠኝነት ሽልማት ተሰጣቸው።
የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ መስራችና ስራ አስኪያጅ #መዓዛ_ብሩ ሽልማቱ የተሰጣቸው የኢጋድ(IGAD) ዓመታዊ የሚዲያ ሽልማት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በተካሄደበት ወቅት ነው።

ሽልማቱንም ከኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስና ከኢጋድ ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር ) ተቀብለዋል።

ኢጋድ በየዓመቱ በተለያዩ ዘርፎች የአባል ሀገራትን የተመለከቱ ዘገባ የሰሩ ጋዜጠኞችን የሚሸልም ሲሆን ዘንድሮም የአየር ንብረት ለውጥን የተመለከቱ ዘገባዎች የሰሩ ጋዜጠኞች ስራ አወዳድሮ ሸልሟል።
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp https://tinyurl.com/ycxjmm3s








