top of page

መጋቢት 24፣2016 - ''የግልግል ተቋም'' በዓመት እስከ 5 ቢለዮን ብር ግምት ያላቸውን ንግድ ነክ አለመግባባቶች ተመልክቶ ውሳኔ እየሰጠ ነው ተባለ

  • Apr 2, 2024
  • 1 min read

በአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ስር የተደራጀው የግልግል ተቋም በዓመት እስከ አምስት ቢለዮን ብር ግምት ያላቸውን ንግድ ነክ አለመግባባቶች ተመልክቶ ውሳኔ እየሰጠ ነው ተባለ።


የግልግል ተቋሙ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 26 ንግድ እና ንግድ ነክ የሆኑ አለመግባባቶችን ተመልክቶ ውሳኔ መስጠቱ ተነግሯል።


የአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በስሩ የግልግል ተቋም አደራጅቶ መስራት ከጀመረ ሃያ ሶስት አመታትን አስቆጥሯል።


ተቋሙ ንግድ እና ንግድ ነክ የሆኑ አለመግባባቶች ሲከሰቱ በግልግል እና ከግልገል መለስ ባሉ መንገዶች ውሳኔ እንዲያገኙ ያደርጋል፤ ይህን አገlግሎት የሚሰጠውም የንግድ ምክር ቤቱ አባል ለሆኑምላልሆኑም ነው ሲሉ የአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የግልግል ተቋም ዳይሬክተር አቶ ዮሃንስ ወልደገብርኤል ነግረውናል።


በተቋሙ የሚሰጠው አገልግሎት ከሞላ ጎደል በመደበኛ ፍርድ ቤቶች የሚሰጠው አይነት እንደሆነ ሠምተናል።


የግልግል ተቋሙ በአመት በአማካይ እስከ አምስት ቢሊየን ብር ግምት ባላቸው ንግድ ነክ ውዝግቦች ላይ ውሳኔ እንደሚሰጥ፤ የአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ዋና ፀሃፊ አቶ ሺበሺ ቤተማርያም ተናግረዋል።

በዚህ አመትም 36 ጉዳዮች በተቋሙ እየታዩ እንደሚገኙ ሠምተናል።


ካለፈው አመት የተላለፉትን ጨምሮ 26 አለመግባባቶች ውሳኔ እንደተሰጣቸው የግልግል ተቋም ዳይሬክተር አቶ ዮሃንስ ወልደገብርኤል ነግረውናል።


ንጋቱ ረጋሣ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ በተጠናቀቀው በበጀት አመት 117 ሺህ ህፃናት ተወልደው የልደት ማረጋገጫ ሰጥቻቸዋለው ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ተናገረ፡፡

ሐምሌ 21 2018 በአዲስ አበባ በተጠናቀቀው በበጀት አመት 117 ሺህ ህፃናት ተወልደው የልደት ማረጋገጫ ሰጥቻቸዋለው ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ተናገረ፡፡ ይህም ህፃናቱ ተወልደው በ90 ቀናት ውስጥ የተመዘገቡ ናቸው ሲሉ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ዮሴፍ ንጉሴ አስረድተዋል፡፡ ዘግይተው

 
 
 
ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡

ሐምሌ 21 2018 ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡ የዓሣ ምርቱ ወደ መሃል ሃገር እየተጫነ ለአዲስ አበባ ገበያ እየቀረበ ነውም ተብሏል፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ መገንባቱን ተከትሎ በተፈጠረው ንጋት ሰው ሰራሽ ሃይቅ በኢትዮጵያ ትልቁና ከ70 በላይ ደሴቶች ያሉት የውሃ አካል ነው፡፡ ከቅርብ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page