''ደንብ አስከባሪ ባለሞያዎች በሞያ ስነ ምግባር ታንፀው እንዲሰሩ እያደረግሁ ነው'' የደንብ ማስከበር ባለስልጣን
- 18 hours ago
- 1 min read
Updated: 2 minutes ago
የካቲት 20/2018
ደንብ አስከባሪዎች ህግን በተከተለ መልኩ እና ሞያዊ ስነ ምግባርን ጠብቀው የተሰጣቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ እያደረግሁ ነው ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ በማስከበር ባለስልጣን ተናገረ።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከዚህ ቀደም አልፎ አልፎ በደንብ አስከባሪዎች የሚፈጸሙ የሥነ ምግባር ጥሰቶች አሁን እየቀነሱ ነው ብሏል።
ከዚህ ቀደም ህግን ለማስከበር አልፎ አልፎ በደንብ አስከባሪዎች በኩል ይስተዋሉ የነበሩ የስነ ምግባር ግድፈቶች እንዳይኖሩ እየሰራ መሆኑንም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ተናግሯል።
ደንብ አስከባሪዎች ህግን በተከተለ መልኩ እና ሙያዊ ስነ-ምግባርን ጠብቀው የተሰጣቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ፣ ማህበረሰቡን ስነ-ምግባር በተሞላበት መልኩ እንዲያገለግሉ ለማስቻል የስነ ምግባር ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑን ሰምተናል።
ከዚህ ቀደም አንዳንድ ደንብ አስከባሪዎች በጎዳና ንግድ የተሰማሩ ነጋዴዎችን ሲያንገላቱ፣ ሲደበድቡ፣ ብሎም የያዙትን እቃ ጭምር ሲበታትኑ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በባለሥልጣኑም የደንብ አስከባሪዎች ላይ በህገ-ወጦች ድብደባ እየተፈጸመባቸው ስለመሆኑ ሲናገር ነበር።
ይህው ጉዳይ በተንቀሳቃሽ ምስሎች ጭምር በስፋት በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወር እንደነበር ይታወሳል።
ይህንን የስነ ምግባር ግድፈት ለመፍታትም የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አባላቶቹን በስነ ምግባር የታነፁ ለማድረግ እያሰለጠንኩ ነው ብሏል።
ይህም ስልጠና በአንዳንድ ደንብ አስከባሪዎች የሚፈፀሙ የስነ ምግባር ጥሰቶች እንዲቀንሱ ማድረጉ ተነግሯል።

የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ እና የስልጠናና ቅድመ መከላከል ሀላፊ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ጥቂት በማይባሉ ደንብ አስከባሪዎች ላይ የሚስተዋለውን የስነ ምግባር ጥሰት መከላከልና መቀነስ የሚቻለው የእርምት እርምጃ በመውሰድ ብቻ ባለመሆኑ አባላቶችን በስነ-ምግባር ለማነፅ የስነ ምግባር ስልጠናው እንዲጀምር ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።
ስልጠናውም ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጋር ውል በመግባት መሰጠት እንደጀመረ ነግረውናል።
በከተማው የሚፈፀም የደንብ ጥሰት 87 በመቶ መቀነሱንም ባለስልጣኑ ነግሮናል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የስነ ምግባር ጥሰት ፈጽመዋል ባላቸው 18 ደንብ አስከባሪዎች ላይ ከደመወዝ ቅጣት እስከ ስራ ማገድ እርምጃ መውሰዱንም ተናግሯል።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
ፍቅሩ አምባቸው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments