top of page

የካቲት 28፣2016 - በዓለም አቀፍ ደረጃ በገዳይነቱ 4ኛ ደረጃን የሚይዘው የማህፀን በር ካንሰር በየዓመቱ 342 ሺህ ሴቶችን ይገድላል ተባለ

  • Mar 7, 2024
  • 1 min read

በዓለም አቀፍ ደረጃ በገዳይነቱ 4ኛ ደረጃን የሚይዘው የማህፀን በር ካንሰር በየዓመቱ 342 ሺህ ሴቶችን ይገድላል ተባለ፡፡


በየዓመቱ በበሽታው የሚጠቁ ሴቶች ቁትርም 604 ሺህ ነው ተብሏል፡፡


ይህንን ያለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ነው፡፡


90 በመቶ የሚሆኑት የበሽታው ተጠቂዎች በመካከለኛ እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ ናቸው ያሉት የቢሮው ሃላፊ ዶክተር ዮሀንስ ጫላ በተለይም ችግሩ ከሰሀራ በስተደቡብ ባሉ የአፍካ ሀገራት በስፋት ይስተዋላል ብለዋል፡፡


በዚህም በአለም ላይ በአማካይ በየሁለት ደቂቃው አንዲት ሴት በማህፀን በር ካንሰር ህይወቷን እንደምታጣ ተነግሯል፡፡


በኢትዮጵያም ከጡት ካንሰር ቀጥሎ በገዳይነቱ ሁለተኛ ደረጃን የያዘ እንደሆነ እና በአመት 5,000 ሴቶች እንደሚሞቱ ሲነገር ሰምተናል፡፡


ፋሲካ ሙሉወርቅ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
በመንግሥት አደረጃጀት እና ቅርፅ አጀንዳ ሥር ሲመክሩ የቆዩ የሥራ ቡድኖች ከ53 ንዑሳን ጉዳዮች ውስጥ በ50ው ላይ ተስማምተው ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ተሻግረዋል።

በመንግሥት አደረጃጀት እና ቅርፅ አጀንዳ ሥር ሲመክሩ የቆዩ የሥራ ቡድኖች ከ53 ንዑሳን ጉዳዮች ውስጥ በ50ው ላይ ተስማምተው ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ተሻግረዋል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ ተመካካሪ፤ ሦስት ንዑሳን አጀንዳዎች ግን ለአስማሚ ግብረ ኃይል ይላካሉ መባሉን ነግረውናል። ወደ አስማሚ ግብረ ኃይል ይላካሉ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page