የሃይማኖት ጉዳዮች እና የሰላም ግንባታ አጀንዳ ተመካካሪዎች ባቀረቧቸው ምክረ ሀሳቦቻቸው ላይ መግባባታቸውን የምክክር ኮሚሽን ይፋ አደረገ፡፡
- 4 hours ago
- 1 min read
ነሐሴ 5 2018
የሃይማኖት ጉዳዮች እና የሰላም ግንባታ አጀንዳ ተመካካሪዎች ባቀረቧቸው ምክረ ሀሳቦቻቸው ላይ መግባባታቸውን የምክክር ኮሚሽን ይፋ አደረገ፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እያካሄደ ባለው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በኮሚሽኑ ምክር ቤት በተለዩ ስምንት አጀንዳዎች ላይ ምክክር እየተደረገ ነው፡፡
አጀንዳዎቹ 500 አባላት ባሏቸው ስምንት የስራ ቡድኖች ምክክር እየተደረገባቸው ይገኛሉ፡፡

በኮሚሽኑ የአሰራር ሥነ-ዘዴ መሰረት 500 አባላት ያሉት አንድ ቡድን በአንድ አጀንዳ ላይ እየተመካከረ ነው፡፡
በዚህም በሃይማኖት ጉዳዮች እና በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ለይ ሲመካከሩ የቆዩት ሁለት ቡድኖች ዛሬ ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በተጠናቀሩ ምክረ ሀሳቦቻቸው ላይ ተስማማተው በተዘጋጀው ቃለ ጉባኤ ላይ ተፈራርመዋል ሲል ኮሚሽኑ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል፡፡
ይሁንና ኮሚሽኑ ተመካካሪዎች የተስማሙባቸውን ወይንም ያቀረቡዋቸውን ምክረ ሀሳቦችን አልዘረዘረም።
የሌሎች አጀንዳ ተመካካሪዎችም በቀጣይ ቀናት በተመሳሳይ መልኩ የአጀንዳ ሀሳቦቻቸውን የጋራ አድርገው በቃለ ጉባኤዎቻቸው ላይ በመፈራረም ይስማማሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲልም ኮሚሽኑ አስረድቷል፡፡
_edited.jpg)



Comments