top of page

የኦሮሚያ ሕብረት ስራ ባንክ ከ20.5 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች ባለው በኮፔይ ኢ - ብር እስካሁን ከ4.8 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይት መፈጸሙን ተናገረ።

  • sheger1021fm
  • 9 minutes ago
  • 1 min read

ጥር 6/2018


የኦሮሚያ ሕብረት ስራ ባንክ ከ20.5 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች ባለው በኮፔይ ኢ - ብር እስካሁን ከ4.8 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይት መፈጸሙን ተናገረ።


ባንኩ ከውጭ ሀገር የሚላክላቸውን የውጭ ምንዛሬ ከባንኩ በኩል ለተቀበሉ ደንበኞቹ ባዘጋጀው የውጭ ምንዛሪ የሎተሪ እድለኞችን ሸልሟል፣ ዲጂታል ሎተሪ ሽያጭ እንደሚጀምር ተናግሯል።


የተላከላቸውን የውጭ ሀገር ገንዘብ ከኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ በመቀበላቸው እድለኛ የሆኑ ደንበኞች አንድ ዘመናዊ የቤት መኪና፣ 2 የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል ፣10 ላፐቶፖች፣ 10 ቴሌቪዥኖችና 40 ስማርት ስልኮች በአጠቃላይ 63 ሸልማቶች ዕድለኞች ተበርክተዋል።

የባንኩ ኦፕሬቲንግ ተጠባባቂ ቺፍ አፊሰር አቶ አብዲ ፈቀደ ባንኩ ከኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎትና ታምሶል ኮሚዩኒኬሽን ጋር በመተባበር፣ በኮፔይ ኢ-ብር ሞባይል ዋሌቱ፣ የዲጂታል ሎተሪ ሽያጭ እንደሚጀምር ተናግረዋል።


ከ20.5 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች ባለው በኮፔይ ኢ-ብር እስካሁን ከ4.8 ትሪሊዮን ብር በላይ የሚገመት ግብይት መፈጸሙን አስረድተዋል።


ባንኩ እንደ ሀገር በተያዘው 2030 ወደ ዲጂታል ሽግግር ሂደት ከፍተኛ ተሳትፎ በማድረግ ላይ የሚገኝ መሆኑን በመጠቆም፣ በኮፔይ ኢ-ብር ዲጂታል ሎተሪ ሽያጭ የመጀመሩ እንቅስቃሴም የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል።


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…..


X : https://x.com/shegerfm?s=2

Website፡ https://www.shegerfm.com/

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page