የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የግብርና ምርቶች በእሴት ጭመራ እና የማምረቻ ዋጋ መቀነስ ካልተቻለ ተወዳዳሪ እንዳንሆን ሊያደርገን ይችላል ሲሉ አግሮ ኢኮኖሚስት አስጠነቀቁ፡፡
- 1 hour ago
- 2 min read
ሚያዝያ 28/2018
የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የግብርና ምርቶች በእሴት ጭመራ እና የማምረቻ ዋጋ መቀነስ ካልተቻለ ተወዳዳሪ እንዳንሆን ሊያደርገን ይችላል ሲሉ አግሮ ኢኮኖሚስት አስጠነቀቁ፡፡
የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የገቢያ አቅሙ በባለሙያዎች ሲመዘን 1.4 ቢሊዮን ህዝብን ታሳቢ ያደረገ ሲሆን 3 ትሪሊዮን ዶላር በአህጉሪቱ ውስጥ እንዲዘዋወር ያደርጋል፡፡
አፍሪካዊያን በንግዱ ስርዓታቸው እሴት መጨመር ላይ ትኩረት አድርገው የማይሰሩ ከሆነ ዋንኛው የዚህ ነፃ ንግድ ቀጠናው ፈታኝ ችግር ይህ ሊሆን ይችላል ተብሏል፡፡
ታደለ ማሞ(ዶ/ር) አግሮ ኢኮኖሚስት ሲሆኑ በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የግብርና ኢኮኖሚ ምርምር ዳይሬክተር ናቸው፡፡ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ለኢትዮጵያ ግብርና እድልም ስጋትም ይዞ ይመጣል ይላሉ፡፡
ምርቶችን በትክክል ካመረትንና በስፋት ከሰራን በአነስተኛ ወጪ ለምርቶቻችን ገበያ ማግኘት እንችላለን ብለዋል፡፡

በነፃ ገበያው የታሪፍ ቅናሽ ይኖረዋል ለገበያ ምርቶች ስናቀርብ በተሸከርካሪ ወደ አንዳአንድ ሀገራት በአንድ ቀን የማድረስ እድል ይኖራል እነዚህ ሁሉ ጥሩ እድሎች ይዘውልን ይመጣሉ ሲሉም ነግረውናል፡፡
ይህ መሆኑ ደግሞ በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እንዲጨምርና የአህጉሪቱ ባለሃብቶች አፍሪካ ውስጥ የበለጠ እንዲያመርቱ ውጤታማ እንዲሆኑ ሊያደርግ ይችላል በማለት ያስረዳሉ፡፡
ለኢትዮጵያ ይህ የንግድ ትስስር ስጋቶች ሊኖሩን እንደሚችል ይናገራሉ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የማምረቻ ዋጋ ከፍተኛ ነው የሚሉት ዶክተር ታደለ ማሞ የቴክኖሎጂ አጠቃቀማችን ከሌሎች ጋር ሲወዳደር ገና ብዙ ይቀረናል ብለዋል፡፡
በዚህ ምክንያት የሀገር ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶች የእኛን ምርቶች እንዳይውጣቸው ስጋት አለ ሲሉም ጠቅሰዋል፡፡
ኢትዮጵ ከአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ገበያ ተጠቃሚ ለመሆን የመሰረተ ልማት ስራው ላይ መበርታት አለባት ይላሉ አግሮ ኢኮኖሚስቱ ዶክተር ታደለ ማሞ፡፡
ከዚህ ባለፈም እሴት መጨመሩ ላይ ከወዲሁ በርትተን መስራት አለብን ያሉ ሲሆን ኢትዮጵ ውስጥ በምርት ላይ እየደባለቁ የመሸጡ አባዜ ወደ አፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠናው ነጋዴው ይዞ እንዳይመጣ በጥራት ላይ ብርቱ ስራ መሰራት አለበትም ብለዋል፡፡
ኢትዮጵ በግብርናው ዘርፍ የበለጠ ተወዳዳሪ ለመሆን ከፈለገች ከሌሎች ሀገራት የበለጠ ምን ማምረት እንዳለባት በመለየት በዚያ ምርት ላይ አተኩሮ መስራቱ ሊበረታታ ይገባል ሲሉም መክረዋል፡፡
ምርቱ ከሀገር ከመውጣቱ በፊት በቂ የጥራት ቁጥጥር መደረግ አለበት ለዚህ ይረዳ ዘንድም የጥራት መቆጣጠር አሰራሩን ማጠናከር ይገባልም ተብሏል፡፡
ሙሉውን ለማድመጥ…
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments