የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ 100ሚሊዮን ብር ወጪ ያደረገበትንና የቁጥጥር ባለሙያዎቹን የሚከታተልበት ቴክኖሎጂ ወደ ስራ ማስገባቱን ተናገረ።
- sheger1021fm
- 4 hours ago
- 1 min read
ህዳር 24 2018
የአዲስ አበባገቢዎች ቢሮ 100ሚሊዮን ብር ወጪ ያደረገበትንና የቁጥጥር ባለሙያዎቹን የሚከታተልበት ቴክኖሎጂ ወደ ስራ ማስገባቱን ተናገረ።
ግብር ከፋዮችን ለመከታተል የሚሰማሩ የመስሪያ ቤቱ የቁጥጥር ባለሙያዎችን ካሜራ የተገጠመበት የደምብ ልብስ አልብሶ ማሰማራቱን ቢሮው ዛሬ ጋዜጠኞችን ጠርቶ በሰጠው መግለጫ ተናግሯል።
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ወደዚህ ስራ የተገባበትን ምክንያት ሲያስረዱ የቁጥጥር ባለሙያዎች ያለ አግባብ ይቀጡናል፤የእጅ መንሻ እንድንሰጥ ይደራደሩናል የሚሉና ሌሎችም ቅሬታዎች ተደጋግመው ከግብር ከፋዩ የሚመጡ በመሆኑ ለዚህ ምላሽ ለመስጠት ነው ብለዋል።

ባለሙያዎቹ የሚለብሱት ካሜራ የተገጠመበት የደምብ ልብስ በቀጥታ በማዕከል ከተተከለው የቁጥጥር ካሜራ ጋር የተገናኘ ነው የሚሉት አቶ ቢኒያም፤ ባለሙያዎቹ የት እንደተመደቡ፣ከግብር ከፋዩ ጋር የሚያደርጉት ንግግር በድምፅና በምስል በቀጥታ ከማዕከል ክትትል የሚደረግበት መሆኑን አስረድተዋል።
በመሆኑም ከዚህ በኋላ ለቁጥጥር ወደግብር ከፋዩ የሚመጡ ባለሙያዎች በካሜራ እይታ ውስጥ ሆነው የሚሰሩ በመሆኑ ያለ አግባብ ተቀጣሁ፣ ስራዬን እንዳልሰራ አድርገውኛል የሚል ግብር ከፋይ ካለ የተቀረፀው ቪዲዮ እየታየ መልስ የሚሰጥበት አሰራር ይኖራልም ተብሏል።
በሁሉም ቅርንጫፎች ያሉ 800 ያህል የገቢዎች ቢሮ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለዚህ ስራ መሰማራታቸውን ሃላፊው አቶ ቢኒያም ጠቅሰው ለግብር ከፋዩ ቅሬታ እፎይታን የሚሰጥ ነው ያሉት ይህ ቴክኖሎጂ በኢንሳ አማካኝነት የለማ ነው ማለታቸውንም ሰምተናል።
ምንታምር ፀጋው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp https://tinyurl.com/ycxjmm3s








