የአውሮፓ ህብረት በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት አቋርጦት የነበረውን የበጀት ድጋፍ ዳግም አስጀመረ።
- 2 hours ago
- 1 min read
ሚያዝያ 12/2018
የአውሮፓ ህብረት በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት አቋርጦት የነበረውን የበጀት ድጋፍ ዳግም አስጀመረ።
በዚህም ህበረቱ ለኢትዮጵያ መንግስት የበጀት ድጋፍ 140 ሚሊዮን ዩሮ ለመስጠት መወሰኑን የአውሮፓ ህብረት የአለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽር ጆሴፍ ሲኬላ ተናግረዋል።
ኮሚሽነሩ ይህንን የተናገሩት በአዲስ አበባ መካሄድ በጀመረው የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ህብረት የቢዝነስ ፎረም ላይ ነው።
የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የበጀት ድጋፍ መስጠቱን ያቋረጠው ከስድስት አመት በፊት እ.አ 2020 እንደነበር ተጠቅሷል።
ህብረቱ የበጀት ድጋፍ ማድረጉን ዳግሞ ያስጀመረው የኢትዮጵያ መንግስት እየወሰዳቸው ያሉ ሪፎርሞች ላይ እምነት ስለሳደረ ነው ሲሉ ኮሚሽነሩ አስረድተዋል።
በሌላ በኩል የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ የንግድ ቀጠናን ተግባራዊት ለማፍጠን የሚያግዝ 1.2 ቢሊዮን ዮሮ ድጋፍ ስምምነትም በፎረሙ ላይ ተፈርሟል።

300 የሚጠጉ የአውሮፓ ሀገራት ኩባንያዎች በተለያዩ ዘርፎች በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ በኢንቨስትመንት ላይ ናቸው ተብሏል።
የቢዝነስ ፎረሙ የአውሮፓ እና የኢትዮጵያ የንግድ ተቋማት፣ ባለሀብቶች እና ተቋማት በአንድ ላይ ያገናኘ ሲሆን የንግድ እና ኢንቨስትመንት ግንኙነቶችን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ተጠቅሷል።
በዚህም የግብርና ንግድ ፣ ንፁህ ኢነርጂን፣ ጤናን እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ጨምሮ እድሎችን ፎረሙ ያጎላል ተብሎ ተገምቷል።
በአሁኑ ገዜ በኢትዮጵያ ወደ 300 የሚጠጉ የአውሮፓ ኩባንያዎች በሀገሪቱ ውስጥ መዋዕለንዋያቸውን ፈሰሱ እያደረጉ ሲሆን ይህም የአውሮፓ ህብረት እና የኢትዮጵያ የንግድ ግንኙነት ከ 2014 ዓ.ም ወዲህ በአሁኑ ጊዜ በጣም ጠንካራ ነው ሲባል ሰምተናል።
ፎረሙ ሁለት ቀን ተኩል ይቆያል።
ንጋቱ ሙሉ

