የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ በተለያዩ ሀገሮች ተመድበው ሲሰሩ የቆዩ 29 የሀገሪቱን አምባሳደሮች ወደ አገር ቤት አስጠሯቸው፡፡
- sheger1021fm
- 2 days ago
- 1 min read
ታህሳስ 14/2018
የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ በተለያዩ ሀገሮች ተመድበው ሲሰሩ የቆዩ 29 የሀገሪቱን አምባሳደሮች ወደ አገር ቤት አስጠሯቸው፡፡
ወደ አገር ቤት የተጠሩት አምባሳደሮቹ በአፍሪካ ፣ በእስያ ፣ በምስራቅ አውሮፓ እና በላቲን አሜሪካ አገሮች ተመድበው ሲሰሩ የቆዩ መሆኑን AOL ፅፏል፡፡

ትራምፕ በ47ኛ ፕሬዘዳንትነት ወደ ዋይት ሐውስ እንደተመለሱ በቀድሞው ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን የአስተዳደር ዘመን ተሾመው የነበሩ በርካታ አምባሳደሮችን እንዳባረሩ መረጃው አስታውሷል፡፡
ፕሬዘዳንቱ 29 አምባሳደሮችን ላባረሩበት እርምጃ የዋይት ሐውስ ሹሞች ይሄ የተለመደ አሰራር ነው ማለታቸው ተሰምቷል፡፡
ትራምፕ የአሜሪካ ትቅደም አጀንዳቸውን የሚያራምዱላቸውን መርጠው የመሾም መብታቸው የተጠበቀ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ከየሀላፊነታቸው የሚነሱት አምባሳደሮች በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ባልደረባነታቸው ግን አይባረሩም ተብሏል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1












Comments