top of page

የተሰጠው የስራ ጊዜ ሲጠናቀቅ 2 ሳምንት የቀረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል አለ፡፡

  • sheger1021fm
  • 4 minutes ago
  • 1 min read

ጥር 29/2018


የተሰጠው የስራ ጊዜ ሲጠናቀቅ 2 ሳምንት የቀረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል አለ፡፡


የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም የተሰጠው ጊዜ ገደብ የሚጠናቀቀው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን "የጀመርኩት ስራ ተንጠልጥሎ እንዳይቀር " ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል ብሏል።


መሰረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ተነጋግሮ መፍትሄ ለመስጠት በ2014 ዓ.ም እና አላግባብ ብለው በቆዩ ሃገራዊ የተቋቋመው የምክክር ኮሚሽን መጀመሪያ የተሰጠው የጊዜ ገደብ 3 ዓመት ነበር።


በሰላም እጦት፣ በፖለቲካ አለመረጋጋት እና በተለያዩ ምክንያቶች በተሰጠው 3 ዓመት ተልዕኮውን ማጠናቀቅ ባለመቻሉ የህዝብ እንዳራሴዎች ምክር ቤት የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው አስቸኳይ ሰብሰባ ነበር የኮሚሽኑን የስራ ዘመን በአንድ ዓመት ያራዘመው።

ኮሚሽኑም በተሰጠው የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከአማራ ክልል ፣ ከትግራይ ክልል፣ ከታጣቂዎች ፣ በተለያዩ አገራት ከሚገኙ ኢትዮጵያዊን (ዲያስፖራዎች) ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና እስረኞች አጀንዳዎች እንደሚሰበሰብ እና የምክክር ጉባዔን አድርጎ እንደሚያጠናቅቅ ተናግሮ ነበር።


የምክክር ኮሚሽን እስካሁን አቅዶት ከነበረው ወስጥ ከትግራይ ክልል አጀንዳ ፣ ከእስረኞች ፣ በከፊል ከታጣቂዎች እና ከተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች አጀንዳዎችን በእቅዱ መሰረት መረከብ እንዳልቻለ ተናግሯል።


ከኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች አንዱ የሆኑት ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ ኮሚሽኑ እስካሁን ድረስ ከ11 ክልሎች ፣ ከሁለቱ ከተማ አስተዳደር እና ዲያስፖራዎች አጀንዳዎችን መረከባቸውን አስታውሰው ፤ ይሁንና ኮሚሽነሩ ከትግራይ ከእስረኞች እና ከታጣቂዎች አካላት አጀንዳ ስላልተሰበሰበ እንዲሁም የምክክር ጉባዔው ስላልተካሄደ ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገናል ሲሉ ነግረውናል፡፡

ኮሚሽኑ ተጨማሪ ጊዜ የሚያስፈልገኝ የተሰጠኝ ሀላፊነት በአግባቡ እንድከውን ነው ብሏል፡፡


ኮሚሽነሩ በትግራይ ክልል ያለው የፖለቲካ አለመረጋጋት እና በጊዜአዊ አስተዳደሩ የሚቀመጡ ቅደመ ሁኔታዎች ኮሚሽኑ በእቅድ መሰረት እንዳይሰራ አድርጓል ሲሉ አስረድተዋል።


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page