top of page

የስራ ስምሪት ወደተደረገባቸው ሀገራት ሰራተኞች እየሄዱ ነው፡፡

  • Jun 17
  • 1 min read

ሰኔ 10/2018


የስራ ስምሪት ወደተደረገባቸው ሀገራት ሰራተኞች እየሄዱ ነው፡፡


አሁንም ግን በደላሎችና በኤጀንሲዎች ተታለው ወደ ውጪ ለስራ በህገ-ወጥ መንገድ የሚሄዱ አሉ፡፡


የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ይህንን ለማስቆም ምን እየሰራ ነው?


ህገ-ወጥ ስደትን ለመከላከል የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከተለያዩ የሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ማለትም ከፍትህ ሚኒስቴር ፣ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከፌዴራል ፖሊስ ከኢሚግሬሽ እና ዜግነት አገልግሎት ጋር በጋር እየሰራ እንደሆነ ተናግሯል፡፡


በህገ ወጥ መንገድ ካናዳ እንልካችኋን እየተባሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች እየተጭበረበሩ እንደሆነ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተናግሯል፡፡


ኢትዮጵያ ወደ ካናዳ የሰለጠነ የሰው ኃይል ለመላክ ስምምነት አድርጋለች ወይ? ካደረገች የስራ ስምሪት እየተደረገ ነው ወይ ? ስንል ጠይቀናል፡፡


በስራና ክህሎት ሚኒስቴር የውጭ ሃገር የስራ ስምሪት ዴስክ ሃላፊ አቶ በዛብህ ከተማ ካናዳ ከሚገኝ አንድ ተቋም ጋር ስምምነት ተፈረመ እንጂ የስራ ስምሪት አልተጀመረም ሲሉ ነግረውናል፡፡


የስራ ስምሪት ሲጀመር መንግስት በሚዲያ ያሳውቃል እስከዛ ከመጭበርበር እና ገንዘባችሁን ከመበላት እራሳችሁን ጠብቁ ብለዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…

ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…









 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page