ከክልሎች ጋር በመተባበር 1 ሺህ 452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት ማቀዱን የትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ።
- 1 hour ago
- 1 min read
ሚያዝያ 20/2018

ከክልሎች ጋር በመተባበር 1 ሺህ 452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት ማቀዱን የትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ።
አዲስ የሚገነቡት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ727 ወረዳዎች ውስጥ ነው ተብሏል፡፡
626 ትምህርት ሚኒስቴር የሚገነባ ሲሆን ቀሪው ደግሞ ክልሎች እራሳቸው እንደሚገነቡ ተነግሯል።
ለዚህ ስራ የሚያስፍልገው 40 ሚሊዮን ዶላር ከአጋር ድርጅቶች እርዳታ ተገኝቷል ተብሏል።
እስካሁን 460 የሚሆኑ ኮንትራክተሮች የተመረጡ ሲሆን ቀሪው ደግሞ በሚቀጥሉት ጊዜያት ለመፈለግና በዚህ አመት ግንባታው አጠናቆ በ2019 ወደ ስራ ለመግባት መታቀዱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።
ይህ ስራ ሲጠናቀቅ 87 ሺ አዲስ ተማሪዎች ወደ ትምህርት እንዲቀላቀሉ ያደርጋል ተብሏል።
በሌላ በኩል የትምህርት ሚኒስቴር 36 ሚሊዮን የአንደኛ ደረጃ መፅሐፍትን ለማሳተም የመጨረሻ ደረጃ ላይ መድረሱን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስረድተዋል ። መፅሐፍቱ ለመጪው የትምህርት ዘመን ይደርሳል ያሉ ሲሆን በዚህ አመት 23 ሚሊዮን የአንደኛ ደረጃ መፅህፍት ማሳተሙና ማከፋፈሉን ተነግሯል።
በዚህ ስራም የመፅሐፍት ተማሪ ጥምርታው በአዲሱ የትምህርት አመት ወደ አንድ ለአንድ ይደርሳል ተብሏል።
በረከት አካሉ




Comments