ከህግ ውጪ ታስረው የነበሩ ከ1300 በላይ እስረኞችን ማስለቀቁን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ተናገረ፡፡
- 2 hours ago
- 1 min read
የካቲት 17/2018
ከህግ ውጪ ታስረው የነበሩ ከ1300 በላይ እስረኞችን ማስለቀቁን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ተናገረ፡፡
ኮሚሽኑ ይህንን ያለው ጋዜጠኞችን ጠርቶ አሳሳቢ የሰብዓዊ መብት አያያዞችንና ጠቅለል ያሉ ስራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ በሰጠበት ወቅት ነው፡፡
በኢትዮጵያ ከህግ ውጪ በዘፈቀደ የሚደረግ እስር መኖሩንና ይህም የሰዎችን ህገ መንግስታዊ መብት የሚፃረር በመሆኑ ተደጋጋሚ ውትወታዎችን ሲያደርግ መቆየቱን ኮሚሽኑ ጠቁሟል፡፡

በዚህም በተያዘው ዓመት ከህግ ውጪ የሆነ እስር የመቀነስ አዝማሚያ አሳይቷል ያሉት የሰብኣዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ፤ባደረግነው ውትወታ 130 በላይ በዘፈቀደ ታስረው የነበሩ ሰዎችን አስለቅቀናል ብለዋል፡፡
ከኦሮሚያ ክልል 915 ሰዎች ተለቅቀዋል፤በአማራ ክልል 186፣በሶማሌ ክልል 123፣ በጋምቤላ ክልል 66 እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 46 በድምሩ 1336 በህገወጥ መንገድ ተይዘው የነበሩ ሰዎች ተለቅቀዋል ተብሏል፡፡
ኮሚሽነሩ አቶ ብርሃኑ በተጨማሪም 122 ሰዎች በዋስተና እንዲለቀቁ ማድረጋቸውንና ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ እንዲሁ ታስረው የነበሩ 119 ሰዎች ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ስለማስረጋቸውም አንስተዋል፡፡
በሌላ በኩል የህግ ታራሚዎች የቀን ፍጆታ በጀት የወቅቱን የገበያ ሁኔታ ያገናዘበ አንዲሆን በተደረገው ውትወታ የተወሰነ ማስተካከያ ቢደረግም የታራሚዎቹ የበጀት ጉዳይ አሁንም ችግር ሆኖ መቀጠሉን ከሃላፊው ሰምተናል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7

