ኢዮብ ተስፋ ለሕጻናትና ለወጣቶች በጎ አድራጎት ድርጅት፤ ለ3 የህክምና ተቋሞች የህክምና ቁሳቁሶችን አስረከበ።
- 1 hour ago
- 1 min read
ሚያዝያ 28/2018
ኢዮብ ተስፋ ለሕጻናትና ለወጣቶች በጎ አድራጎት ድርጅት፤ ለ3 የህክምና ተቋሞች 180 ሺህ ዶላር ወይም ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምና ቁሳቁሶችን አስረከበ።
ድርጅቱ ለልብ ህክምና አገልግሎት የሚውሉትን የህክምና ቁሳቁሶቹ ያስረከበው ለጥቁር አንበሣ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ ለቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም የህክምና ኮሌጅ እና ለኢትዮጵያ ልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል ነው።

ኢዮብ ተስፋ ለሕጻናትና ለወጣቶች በጎ አድራጎት ድርጅት ከደጋፊዎቹ ባገኘነው ደጋፍና ትብብር የገዛናቸውንና አብረውት ከሚሰሩ የልብ ሐኪሞች ትብብር ከሜድትሮኒክ ኩባንያ ያገኘናቸውን በጠቅላይ 180,000 ዶላር ወይም ከ27 ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር በላይ የሚያወጡ የሕከምና ቁሳቁሶችና መሳሪያዎችን ለሶስቱ ተቋሞች አስረክቧል።
ኢዮብ ተስፋ ለሕጻናትና ለወጣቶች በጎ አድራጎት ድርጅት በድንገተኛ የልብ ሕመም በ17 ዓመቱ እድሜው ሕይወቱ ባለፈው በኢዮብ አበባው ስም በወላጆችና በወዳጅ ዘመድ ትብብር የተቋቋመ በጎ አድራጎት ድርጅት መሆኑን ሰምተናል።
የበጎ አድራጎት ድርጅቱ ከ4 በፊት የተቋቋመው በሀገረ አሜሪካ ሲሆን በኢትዮጵያም የተመዘገበ ድርጅት እንደሆነ ተነግሯል።
የበጎ አድራጎት በተለይ በኢትዮጵያ በልብ ሕመም ለሚሰቃዩ ልጆችና ወጣቶች ቅድሚያ በመስጠት ነፍስ አድን የሆኑ የሕከምና ቁሳቁሶችንና መሳሪያዎችን በማቅረብ ላይ በርትቶ እየሰራ እንደሆነ የድርጀቱ መስራችና የእዮብ ወላጅ አባት አቶ አበባው አንበሣው አስረድተዋል።
ድርጅቱ ለጥቁር አንበሣ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ፣ ለቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም የህክምና ኮሌጅ እና ለኢትዮጵያ ልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል ከዚህ በፊትም የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችን መስጠቱን ሲነገር ሰምተናል።
በድርጅቱ ቀጥተኛ ድጋፍ ብቻ በኢትዮጵያ ልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል ብቻ 100 ህፃናት መታከማቸውን ሰምተናል።
በአጠቃላይም ኢዮብ ተስፋ ለሕጻናትና ለወጣቶች በጎ አድራጎት ድርጅት ለሶስቱ ህክምና ተቋሞች ባደረገው ድጋፍ የበርካታ ህፃናት ልብ መታከሙን የየሆስፒታሎቹ ሀላፊዎች ተናግረዋል፣ ለዚህም ምስጋና አቅርበዋል።
ድርጀቱ ወደፊትም ተመሳሳይ ድጋፎች እንደሚያደርግ ተናግሮ ለዚህም በየትኛውም የአለም ክፍል የሚገኙ ድርጅቶችም ሆኑ ግለሰቦች እጃቸውን እንዲዘረጉለት ጠይቋል።
ንጋቱ ሙሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7




Comments