''ኢትዮጵያን የትኛውም ትንኮሣ ከጀመረችው የብልፅግና ጉዞ አያስቆማትም'' ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።
- sheger1021fm
- 22 minutes ago
- 1 min read
ህዳር 29 2018
''ኢትዮጵያን የትኛውም ትንኮሣ ከጀመረችው የብልፅግና ጉዞ አያስቆማትም'' ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።
የሚገጥመንን እያንዳንዱን ፈተና ወደ ዕድል በመቀየር የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን እናደርጋለንም ብለዋል።
20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ፤ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት በሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ነው፡፡
በአከባበሩ ላይ የፌዴራል እና የክልል መንግስታት ከፍተኛ ባለስልጣናት የተገኙ ሲሆን መልዕክቶችም ተላልፈዋል።

የዕለቱ የክብር እንግዳ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባደረጉት ንግግር በዓሉ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚደምቁበት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያውያን መተባበርን እና በአንድነት መቆምን የጋራ ሃብታችን እናድርግ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ በተለያዩ መስኮች የሚደነቁ ውጤቶችን እያስመዘገበች ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ጥረት ለማደናቀፍ በየጊዜው ሙከራዎች እንደሚደረጉም ጠቅሰዋል።
ማንኛውም ትንኮሳ ግን ኢትዮጵያን ከብልፅግና ማቆም አይችልም ሲሉ ተናግረዋል።
የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በበኩላቸው ኢትዮጵያውያን ከጋራ ታሪካችን እና እሴታችን የተቀዳ የጋራ ማንነት ሊኖረን ይገባል ብለዋል።
በዓሉ የመመካከር እና የመወያየት ባሕል በኢትዮጵያ እንዲያድግ ረድቷል ያሉት ደግሞ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው ናቸው።
ንጋቱ ረጋሳ












Comments