አዋሽ ባንክ ለ7 ግብረ ሰናይ ድርጅቶች 25 ሚሊዮን ብር ሰጠ።
- 1 hour ago
- 1 min read
የካቲት 26/2018
አዋሽ ባንክ ለ7 ግብረ ሰናይ ድርጅቶች 25 ሚሊዮን ብር ሰጠ።
ባንኩ ለግብረ ሰናይ ድርጅቶቹ ድጋፉን ያደረገው ያለንበትን የረመዳን ወርን ምክንት በማድረግ ነው።
25 ሚሊዮን ብር ድጋፍ የተደረገላቸው ድርጅቶችም ህጻናትን፣ በአረጋዊያንን እና አካል ጉዳተኞችን በመደገፍና በመንከባከብ ላይ የተሰማሩ መሆናቸው ተጠቅሷል።
ወንድም ካሊድ ፋውንዴሽን፣ የስራ ለና የበጎ አድርጎ ድርጅት፣ ተስፋ አዲስ ፓረንትስ ቻይልድሁድ ሰፖርት ኦረጋናይዜሽን፣ ዘ ችልድረንስ ኸርት ፈንድ ኦፍ ኢትዮጵ፣ እዝነት አካል ጉዳተኛ ህፃናትና ወላጆች መርጃ ድርጅት እና አብደላ ኢብኑ ኡሚ መክቱም ቁራን ማህበር ናቸው ድጋፉ የተደረገላቸው።

አዋሽ ባንክ የ1447ኛውን የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ ትናንት ምሽት በሸራተን አዲስ ሆቴል ባዘጋጀው የኢፍጣር መርሃ-ግብር ላይ ነው ድጋፉን የሰጠው።
ባንኩ አዲስ አበባን ጨምሮ በመላው ሀገሪቱ በ52 ከተሞች ለ2600 አባወራዎች፣ አረጋዊያን እና በአነስተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ሰዎች የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ተናግሯል።
በተጨማሪም በአዲስ አበባ እና በ14 ተለያዩ የክልል ከተሞች ከደንበኞቹ ጋር የኢፍጣር መርሃ-ግብር ማካሄዱን ተናግሯል።
ባንክ ባሉት ከ1,005 በላይ ቅርንጫፎቹ አማካይነት ከ3.5 ሚሊዮን በላይ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞችን ማፍራቱን ጠቁመዋል።
በወለድ ነፃ የፋይናንስ ዘርፍ ብቻ ከ27 ቢሊዮን ብር በላይ የሃላል ፋይናንስ አገልግሎት ማቅረቡም ተነግሯል።
የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው ባንኩ ላለፉት 31 ዓመታት በተለይም በማዕድ ማጋራት፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በስራ ፈጠራ እንዲሁም ለአቅመ ደካሞች የመኖሪያ ቤት ግንባታ ከፍተኛ በጀት በመመደብ በርካታ ስራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል።
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments