top of page

ነሐሴ 7፣2016 - የውጭ ምንዛሪ ግብይት ሱቆች ባለቤት ማን ሊሆን ይችላል?

  • sheger1021fm
  • Aug 13, 2024
  • 1 min read

በአጠቃላይ 45 ሚሊዮን ብር ካፒታል ያላቸው ህጋዊ ፈቃድ ወስደው ለውጭ ምንዛሪ ግብይት ሱቅ እንዲከፍቱ ተፈቅዷል፡፡


ሱቆቹ በመላው ኢትዮጵያ ይከፈታሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡


ጥቁር ገበያውን በማክሰም ረገድ የሚኖራቸውን ተፅዕኖ በተመለከተ እና ከጥቁር ገበያ ውጭ ከባንኮችም መወዳደር የሚጠበቅባቸው የእነዚሁ ሱቆች ባለቤት ማን ሊሆን ይችላል?


በጉዳዩ ላይ የምጣኔ ሐብት ባለሞያ አነጋግረናል፤ ባለሞያው ካነሷቸው ነጥቦች መካከል፤


• ከመስፈርቱ ውስጥ 15 ሚሊዮን ብር ካፒታል እና 30 ሚሊዮን ብር በዝግ አካውንት የሚቀመጥ ካፒታል ያለው ባለሀብት የምንዛሬ ሱቅ ግብይት መክፈት ይችላል፡፡


• በባንኮች ውስጥ ፍላጎትን የሚመጥን የውጭ ምንዛሬ ክምችት እስካልኖረ ድረስ ጥቁር ገበያውን ማክሰም አዳጋች ነው፡፡


• በቂ ካፒታል ካላቸው በጥቁር ገበያው ውስጥ ይሳተፉ የነበሩ በህጋዊ መንገድ የምንዛሬ ሱቅ ለመክፈት እድል ስለሚያገኙ ጥቁር ገበያው እንዲሳካ ህጋዊ ሱቅ እንዲከፍቱ መፍቀዱ እድል ይሰጣል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page