top of page

ነሀሴ 27 2017 - የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ "የትውልድ አሻራ" የተሰኘ የመልካም ምኞት ማስተላለፊያና የገንዘብ መላኪያ አጭር ቁጥር ይፋ ተደርጓል

  • sheger1021fm
  • Sep 2
  • 1 min read

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ዛሬ ያስተዋወቀው አጭር ቁጥር 8120 ሲሆን መርሃ ግብሩም «የትውልድ አሻራ - ዲጂታል የብስራት መልዕክትና ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት" የሚል ስያሜ የተሰጠው መሆኑንም ሰምተናል።


የማስተባበሪያ ጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ዶ/ር አረጋዊ በርሄ የአጭር የፅሁፍ መልዕክት መላኪያ መስመሩ አላማ ሲያስረዱ ህዝቡ በሚልከው መልዕክት አሻራውን ለታሪክ እንዲያስቀመጥ ያለመ ነው ብለዋል፡፡


መልዕክቶቹ ሲላኩ በአንድ መልዕክት ለግድቡ 20 ብር ድጋፍ ማድረግ እንደሚቻልና በመላኪያ ቁጥሩ የሚመጡ አማራጮችን በመምረጥ ከ5 ብር ጀምሮ እስከ መቶ ብር ድረስ ድጋፍ ማድረግ እንደሚቻልም ተናግረዋል፡፡


መርሀ ግብሩ ከዛሬ ነሀሴ 27 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ መስከረም 30 ቀን 2018 የሚቆይ መሆኑንም እወቁት ብለዋል።


ምንታምር ፀጋው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page