top of page

ነሀሴ 19 2017 - የወንዝ ዳር ፕሮጀክቶች እና የኮሪደር ስራን የሚቆጣጠርና የሚመራ ባለስልጣን መስሪያ ቤት ተቋቋመለት

  • sheger1021fm
  • Aug 26
  • 1 min read

የአዲስ አበባን የወንዝ ዳር ፕሮጀክቶች እና የኮሪደር ስራን የሚቆጣጠርና የሚመራ ባለስልጣን መስሪያ ቤት ተቋቋመለት፡፡


እስካሁን የተሰሩና ከዚህ በውሃላም የሚሰሩ የወንዝ ዳርና የኮሪደር ልማት ስራዎችን የሚመራና የሚቆጣጠር የኮሪደርና የወንዝ ዳር ፕሮጀክቶች መቆጣጠርና ማስተዳደር ባለስልጣን ተቋም በከተማ አስተዳደሩ መመስረቱን ሰምተናል።


ለአዲስ አበባ የመጀመሪያው የሆነውና በግንባታ ላይ ያለው ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ መናፈሻ የሚደርሰው የ21.5 ኪ.ሜ የወንዝ ዳር ፕሮጀክት ስራ 90 በመቶ መድረሱንም የአዲስ አበባ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈፃሚና የአዲስ አበባ የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ኮሪደር ልማት ምክትል አስተባባሪ አቶ ዋለልኝ ደሳለኝ ነግረውናል።


እስከ መጪው ጥቅምት ወር መጨረሻም አጠቃላይ ስራው ይጠናቀቃል ተብሏል፡፡


ከዚህ በኋላም ስራውን የሚቆጣጠርና የሚከታተል ተቋም መቋቋሙን ተከትሎም የወንዝ ዳር ፕሮጀክቱ ያለምንም መቆራረጥ በቋሚነት የሚሰራ እንደሚሆንም ተናግረዋል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ....


ቴዎድሮስ ወርቁ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments

Couldn’t Load Comments
It looks like there was a technical problem. Try reconnecting or refreshing the page.
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page