top of page

ነሀሴ 12 2017 - ከተጀመረ ዓመታትን ያስቆጠረው የዩኒቨርሰቲ ኢንዱስትሪ ትስስር ዛሬም የተለያዩ ችግሮች እንዳሉበት ይነገራል

  • sheger1021fm
  • Aug 18
  • 1 min read

ለተግባር ልምምድ የተላኩላቸውን ተማሪዎች ተገኝተዋል ለማለት ብቻ ፊርማ እያስፈረሙ የሚሸኙ ኢንዱስትሪዎች አሉ ተብሏል።


ሌሎቹ ደግሞ ውድ የሆኑ ማሽኖቻችንን ያበላሹብናል በሚል ተማሪዎቹ ወደ ስራው እንዳይቀርቡ ያከላክላሉ ተብለው ተወቅሰዋል ።


ከዚህ በኋላ ግን አሰራሩ ላይ መሰረታዊ ለውጥ እንደሚደረግ ሠምተናል።


ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን ለተግባር ልምምድ ወደ ኢንዱስትሪዎች የሚልኩበት መርሃ ግብር አሁንም የተለያዩ ችግሮች ያሉበት እንደሆነ ተነግሯል።

ree

ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን ለተግባር ልምምድ ወደ ተቋማቱ ሲልኩ መርሃ ግብሩን ለማሟላት እንጂ ማግኘት ስላለባቸው ክህሎት በቂ ዝግጅት አያደርጉም ተብለው ይወቀሳሉ።


ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ለተግባር ልምምድ የሚኩላቸውን ተማሪዎች መከታተልና በአግባቡ ማሰራት ላይ ክፍተት እንዳለባቸው ይነሳል።


በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ስር የሚገኘውን የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትር ትስስር የሚመራው ቡድን አስተባባሪ የሆኑት ኢንጂነር ጌትነት በላይም ይህንኑ ሃሳብ ያጠናክራሉ።


አብዛኞቹ ኢንዱስትሪዎች በደብዳቤ የተመደቡላቸውን ተማሪዎች ተቀብለው በየቀኑ እያስፈረሙ ከመሸኘት ያለፈ ስራ እየሰሩ አይደለም ብለዋል።


ከሚቀጥለው አመት ጀምሮ ግን አሰራሩ እንደሚቀየር ኢንጂነር ጌትነት ነግረውናል።


አንዱ ለውጥ በአብዛኛው በዩኒቨርሲቲዎች ይደረግ የነበረውን የተማሪዎቹን የብቃት ምዘና በኢንዱስትሪዎች እንዲካሄድ ማድረግ ነው ብለዋል።


ከሰባ በመቶ በላዩ የተማሪዎች ምዘና በኢንዱስትሪዎች እንደሚሆን ጠቅስዋል።

ኢንዱስትሪዎች ለተግባር ልምምድ የተላኩላቸው ተማሪዎች ማሽኖችን ያበላሻሉ ወይም ይሰብራሉ በሚል ስጋትም ወደ ስራው እንዳይቀርቡ እንደሚያከላክሉ ተነግሯል።


ውድ የሆኑትን ማሽኖች መተካት የራሳቸው ሃላፊነት ስለነበር ወደ ማከላከሉ እንደገቡ የሚናገሩት ኢንጂነር ጌትነት ከዚህ በኋላ ግን ይህም የእነሱ ብቻ ራስ ምታት አይሆንም ብለዋል።


ከዩኒቨርሲቲዎች በተጨማሪ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትም ተማሪዎቻቸውን ወደ ኢንዱስትሪዎች ልከው የተግባር ልምምድ እንዲወስዱ እንዲወስዱ እንዲያደርጉ የማስተሳሰር ስራ ይሰራል ተብሏል።


ንጋቱ ረጋሳ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page