top of page

ታህሳስ 24፣2016 የጋሞ ዞን አስተዳደር ‘’ኢሰመኮ ትናንት ያወጣውን መግለጫ አልቀበለውም’’ አለ

  • Jan 3, 2024
  • 1 min read

የጋሞ ዞን አስተዳደር ‘’ኢሰመኮ ትናንት ያወጣውን መግለጫ አልቀበለውም’’ አለ፡፡


በጋሞ ዞን አርባ ምርጭ ዙሪያ ወረዳ ውጥረት ተከስቶ የነዋሪዎች ሰብአዊ መብት እየተጣሰ እንደሆነና ለዚህም አስቸኳይ ምላሽ እንደሚሻ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ትናንት ባወጣው መግለጫ ጠይቋል፡፡


ኢሰመኮ በመግለጫው በአካባቢው በተከሰተው ውጥረት የሰው ሕይወት መጥፋትን ጨምሮ ሌሎች የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተፈፅመዋል ማለቱን መዘገባችን ይታወቃል፡፡


ሸገር ከአካባቢው ተፈጥሮአል ስለተባለው ውጥረትና እየደረሰ ነው ስለተባለው የሰብአዊ መብት ጥሰት የዞኑ አስተዳደርን ጠይቋል፡፡


የጋሞ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አባይነህ አበራ ኢሰመኮ ያወጣው ሪፖርት መሰረት የሌለውና በመረጃ ያልተደገፈ ሲሉ ጠርተውታል፡፡


ዞኑ በአሁኑ ሰዓት ሰላም ነው ያሉት ምክትል ዋና አስተዳዳሪው ‘’ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ መንግስት ህግ በሚያስከብርበት ወቅት ሸሽተው ወደ ጋሞ ዞን የገቡ አሉ’’ እነሱንም ቢሆን ክትትል እየተደረገባቸው ነው ብለውናል፡፡


ኢሰመኮ ባወጣው መግለጫ የተፈጠረው ውጥረትን በተመለከተ ከአካባቢው አስተዳደርና የፀጥታ አካላት ጋር ውይይት ሳደርግ ቆይቻለሁ ቢልም የዞኑ ምክትል ዋና አስተዳዳሪ በበኩላቸው ኢሰመኮም ሆነ ማንኛውም የሰብአዊ መብት ተቋም መረጃን ሲያጣራ የዞኑ አስተዳደር ማነጋገር ይገባዋል፤ እስካሁን ድረስ ግን ኢሰመኮም ሆነ ሌላ አካል የጠየቀንም ሆነ ያነጋገረን የለም ብለዋል፡፡


ለመሆኑ በጋሞ ዞን በአርባ ምንጭ ዞሪያ በልዩ ወረዳ እንዋቀር የሚሉ ነዋሪዎች የሉም ወይ ብለን የጠየቅናቸው አቶ አባይነህ ያሉት ተከታዩን ነው፡፡




ማንያዘዋል ጌታሁን ያሰናዳውን በንጋቱ ሙሉ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
የነሐሴ 4 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሳውዲ_አረቢያ በሳውዲ አረቢያ ጂዛን በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ከባድ ቃጠሎ ተቅስቅሶ ነበር ተባለ፡፡ በጂዛኑ ማጣሪያ ላይ ቃጠሎ ተቅስቅሶ የነበረው ከባድ ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡ በጁቢየል የተፈጥሮ ጋዝ ማሰናጃ ከተማም ቃጠሎ ተቀስቅሶ ነበር ተብሏል፡፡ የሳውዲ ምንጮች ቃጠሎዎቹ ተቀስቅሰው እ

 
 
 
በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡

ነሐሴ 4 2018 በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት በበኩሉ ሳያጠፋ የምንቀጣው አሽከርካሪ የለም እንዲያውም ሁሉንም ህጎች እናስከብር ብንል የማይቀጣ አሽከርካሪ አይኖርም ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ምህረት ስዩም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page