top of page

በዓመት በአማካይ እስከ 2,000 ጉዳዮች የመጨረሻ ውሳኔ እንዲያገኙ ለፌዴሬሽን ም/ቤት እየላከ መሆኑን፤ የህገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ተናገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • 32 minutes ago
  • 1 min read

ህዳር 22 2018


በዓመት በአማካይ ከ1,500 እስከ 2,000 ጉዳዮች የመጨረሻ ውሳኔ እንዲያገኙ ለፌዴሬሽን ም/ቤት እየላከ መሆኑን የህገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ተናገረ፡፡

 

የፌዴሬሽን ም/ቤት በዓመት ሁለት ጊዜ ብቻ ስለሚሰበሰብ የሚሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ እንዲዘገይ አድርጎታል ሲልም ጉባኤው ነግሮናል፡፡

 

ጉባኤው ህገ-መንግስታዊ ትርጓሜን የሚሹ አቤቱታዎችን ተቀብሎ በመመርመር የተለያዩ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል፡፡

 

ውሳኔው የመጨረሻ ባለመሆኑ ውሳኔውን በምክረ ሃሳብ መልክ ለፌደሬሽን ምክር ቤት ያቀርባል፤ምክር ቤቱም ጉዳዩን ተመልክቶ የመጨረሻውን ውሳኔ ይሰጣል ሲል ጉባኤው ነግሮናል፡፡

 

ree

አቶ ደበበ ሃይለገብርኤል የህግ ባለሙያና የጉባኤው አባል ናቸው፤ጉባኤው እነዚህን ስራዎች ሲከውን ቆይቷል በዓመትም በአማካኝ ከ1500 እስከ 2000 ጉዳዮችን ተመልክቶ የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥባቸው ወደ ምክር ቤቱ ይመራል ብለውናል፡፡

 

ይሁንና የፌደሬሽን ምክር ቤትን የመጨረሻ ውሳኔ የሚፈልጉ ይህን ያህል ጉዳዮች ቢኖሩም ምክር ቤቱ በዓመት 2 ጊዜ ብቻ የሚሰበሰብ መሆኑና ብዙ ጊዜ የማይቀመጥ መሆኑ ለሚቀርቡ ጉዳዮች የሚሰጠው ውሳኔ እንዲዘገይ ምክንያት ሆኗል ሲሉም አስረድተዋል፡፡

 

ያለፈው 6ኛው ሃገራዊ ምርጫ ይካሄድ አይካሄድ የሚለውን ለመወሰን ህገ መንግስታዊ ትርጉም የተሰጠበት ጉዳይ ላይ የባለሙያዎች ስብስብ የሆነው ጉባኤው ድርሻ እንደነበረውም ያስታውሳሉ፡፡

ree

ሌላኛው የጉባኤው አባል አቶ ምትኩ ማዳ፤ በትግራይ ክልል ከህገ መንግስቱ የሚቃረኑ ህጎች ወጥተዋል የሚሉ  አቤቱታዎች፤ የቤት ኪራይን በተመለከተ በፌድራል መንግስተቱና በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የወጡ መመሪያዎች ህገመንግስታዊ መብትን የሚጥሱ ናቸው የሚሉ አቤቱታዎችም ቀርበውና የጉባኤውን ውሳኔ አግኝተው ለመጨረሻ ውሳኔ ለፌደሬሽን ምክር ቤት የተመሩ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..

ምንታምር

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page