በኢትዮጵያ በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ከአጠላቃይ ህዝቡ 17.3 በመቶው በደም ግፊት ህመም ተጠቂ ሆኖ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
- 15 hours ago
- 2 min read
ግንቦት 12/2018
በኢትዮጵያ በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ከአጠላቃይ ህዝቡ 17.3 በመቶው በደም ግፊት ህመም ተጠቂ ሆኖ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
በዳሰሳው የማህበረሰቡ የጨው አጠቃቀም ከፍ ብሎ ታይቷል፤ ከእንቅስቃሴ የተገደበ አኗኗር እየተለመደ መምጣቱ ችግሩን እንዳያባብሰው ስጋት ፈጥሯል መባሉንም ሰምተናል፡፡
በኢትዮጵያ ከሰው ወደ ሰው የማይተላለፉ በሽታዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ ማህበረሰቡን የማትቃት መጠናቸው እየጨመረ መጥቶ 50 በመቶ የሞት መንስኤዎች መሆናቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡
በሚኒስቴሩ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ዶክተር ህይወት ሰለሞን ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መግቢያ በር ነው የሚባለው የደም ግፊት ህመም ቁጥሩ እየጨመረ መምጣቱን በቅርቡ ያደረግነው የዳሰሳ ጥናት አሳይቶናል ብለውናል፡፡
በዚህም ዳሰሳው በተሰራበት ወቅት ባለው መረጃ መሰረት ከአጠቃላይ የህዝቡ ቁጥር 17.3በመቶዎቹ የህመሙ ተጠቂ ሆነው ተገኛተዋል፤ቁጥሩ ካለፈው ዳሰሳ ጋር ሲመሳከር ከ1 በመቶ በላይ ብልጫ አለው፤የደም ግፊት ህመም የብዙ ሚሊዮኖች ችግር እየሆነ በመምጣቱ ያሳስበናል ብለውናል፡፡
የውስጥ ደዌ ሃኪም የሆኑት ዶክተር ቢኒያም ግርማ በበኩላቸው በዓለም ዙሪያ የህመሙ ተጠቂዎች ቁጥር 1.3 ቢሊዮን ጠቅሰው፤ በዚህ ጨውን አብዝቶ የመመገብ፤ የታሸጉ ምግቦችን አብዝቶ የመመገብና እንቅስቃሴ አልባ የአኗኗር ዘይቤያችን ከቀጠልን አስጊ ስለሚሆን በተለይ በመንግስት በኩል የደም ግፊት ምርመራ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲደረግ አሰራሮች መዘርጋት አለማቸው ይላሉ፡፡
ስለ ምርመራው የጠየቅናቸው በሚኒስቴሩ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈፃሚዋ ዶክተር ህይወት ሰለሞንእውነት ነው ምርመራው ቀላል መሆን አለበት ብለን፤ በመንግስት ስር ባሉ 1500 በሚሆኑ የጤና ተቋማት የደም ግፊት ምርመራን ካርድ ማውጣትና መጠበቅ ሳያስፈልግ እየሰጠን ነው፤ምርመራው በጤና መድህን ስርዓት ውስጥም ተካትቷል ሲሉም ያስረዳሉ፡፡
የዳሰሳ ጥናቱ ሌላው ያካተተው የጨው አጠቃቀምን ነው የሚሉት ዶክተር ህይወት ከገጠር እስከ ከተማ ያለልዩነት የማህበረሰቡ የጨው አጠቃቀም ከፍ ብሎ ታይቷል፤በአንፃሩ የበሽታው አጋላጭ ከሆኑት መንስኤዎች የአልኮልና የትንባሆ አጠቃቀም ላይ መቀነስ መታየቱንም ጠቅሰዋል፡፡
የደም ግፊት በሽታን ለመከላከል የተመከሩ የአኗኗር ዘይቤ ለውጦችን ከማድረግ ባለፈ በየጊዜው ግፊትን መለካት ይገባል ብለዋል ባለሙያዎቹ፡፡
በየዓመቱ ግንቦት 9 ቀን አለም አቀፍ የደም ግፊት ቀን ይከበራል፤ ዘንድሮም የደም ምርመራዎችን በማድረግ ቀኑ መከበሩን ሰምተናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….
ምንታምር ፀጋው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7




Comments