top of page

''በተመደቡበት መስመር ላይ ረዥም ደቂቃ የሚቆሙ አሽከርካሪዎች የመቆጣጠሪያ ዘመናዊ መላ በመጠቀም ክትትል እያደረግሁ ነው'' የአዲስ አበባ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት

  • sheger1021fm
  • 2 hours ago
  • 1 min read

ታህሳስ 10/2018


የአዲስ አበባ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት በተመደቡበት መስመር ላይ ረዥም ደቂቃ የሚቆሙ አሽከርካሪዎችና የተመደቡበትን መስመር በአግባቡ ስለመሸፈናቸው ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ መላ በመጠቀም ክትትል እያደረግሁ ነው አለ።


ድርጅቱ የአገልግሎት ታሪፍ ጭማሪ አድርጓል የሚል ቅሬታ ቢቀርብም የከተማ አውቶብስ ተጠቃሚዎች አንዳንዴ የተራዘመ መስመር ሲጠቀሙ ከተቀመጠው ታሪፍ በተጨማሪ ይከፍላሉ እንጂ የዋጋ ጭማሪ ተደርጎ አይደለም ብሏል።


የአዲስ አበባ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት አዳዲስ በተመሠረቱ የመኖሪያ አካባቢዎች ላይ የሚያጋጥም የትራንስፖርት እጥረት ለማስተካከል የመጠበቂያ ሰዓቱን በማሳጠር የትራንስፖርት አገልግሎቱ እንዲደረስ ለማድረግ ጥረት እያደረግሁ ነው ብሏል።


የአዲስ አበባ የከተማ አውቶብስ ተጠቃሚዎች አንዳንዴ አገልግሎቱን ለማግኘት በአሽከርካሪዎች እንዲሁም በትኬት ቆራጭ ፈቃደኝነት ላይ ተመስርተን ነው የምንገለገለው የሚል ቅሬታ ያነሳሉና ድርጅቱ አሽከርካሪዎቹ መስመራቸውን በአግባቡ ስለመሸፈናቸው ተጠቃሚዎችን አለማንገላታታቸውን እንዴት ይቆጣጠራል ስንል በድርጅቱ የአገልግሎት ዘርፍ ድጋፍ ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ እንዳልካቸው ከበደ ጠይቀናል።

ree

አሽከርካሪ የተመደበበትን መስመር መቀየር አይችልም ስለዚህ የተመደበበት መስመር አለ ያንን መስመሮችን ተከትለን አንቆጣጠራለን በተጨማሪ በአውቶቡሶቹ ላይ ዘመናዊ መቆጣጠሪያ ጂፒኤስ በመግጠም በሰአታቸው እየተንቀሳቀሱ ስለመሆኑ ክትትል ይደረጋል ብለዋል።


ድርጅቱ ምንም ዓይነት የታሪፍ ማሻሻያ አለማድረጉን የነገሩን አቶ እንዳልካቸው በተጠቃሚዎች ፍላጎት የተራዘመ ተጨማሪ ጉዞ ሲኖር ነው የዋጋ ልዩነት እየመጣ ያለው ብለዋል።


በሌላ በኩል ድርጅቱ አዳዲስ የተመሰረቱ መንደሮችና የመኖሪያ አካባቢዎች ላይ ያለን የትራንስፖርት እጥረት ለማሻሻል የመጠበቂያ ሰዓቱን በማሳጠር እንዲሁም የምልልስ መጠኑን በመጨመር የማሻሻያ ስራ እየሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።


የአዲስ አበባ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ከአገልግሎት አሰጣጡ ጋር በተያያዘ ቅሬታ ያለው ማንኛውም ተገልጋይም በተቋሙ የአጭር ቁጥር 8981 በመደወል አቤቱታ ማቅረብ ይችላል አሁንም የሚደረጉ የአገልግሎት ማሻሻያዎችም እየተጨመሩ ይሄዳሉ ብሏል፡፡


ምህረት ስዩም

Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page