በቤት ሰራተኞች እና በአሰሪዎች መካከል ያለውን ግንኙነት ህጋዊ መስመር የሚያስይዝ አዲስ ደንብ እየተዘጋጀ ነዉ ተባለ
- 10 hours ago
- 2 min read
መጋቢት 10/2018
በቤት ሰራተኞች እና በአሰሪዎች መካከል ያለውን ግንኙነት ህጋዊ መስመር የሚያስይዝ እና የህገ-ወጥ ደላሎችን ጣልቃ ገብነት የሚገታ አዲስ ደንብ እየተዘጋጀ ነዉ ተባለ።
በስራና ክህሎት ሚንስቴር እየተዘጋጀ ያለው ይህ ደንብ፣ በቤት ሰራተኞች ላይ የሚደርሱ አካላዊና ስነ-ልቦናዊ ጥቃቶችን ለመከላከል እንዲሁም የአሰሪዎችን መብትና ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ መሆኑ ተነግረሯል።
ብዙ ጊዜ የቤት ሰራተኛ ሲባል ሰዉ የሚገነዘበዉ 70 በመቶ የሚሆኑትን ሴት የቤት ሰራተኞችን ብቻ ቢሆንም በዚህ ደንብ ግን አትክልተኛ፣ ሹፌሮችና ሌሎችም በመኖሪያ ቤት ተቀጥረዉ የሚሰሩ ሰራተኛችን ጭምር እንደሚያካትት ተጠቁሟል።
በሚኒስቴሩ የኢንዱስትሪ ግንኙነትና የስራ ሁኔታዎች ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ጥዑመዝጊ በርሔ አዲሱ ደንብ በቀጣሪም በተቀጣሪም በኩል የሚነሱ ችግሮችና ፈተናዎችን የሚፈታ በተለያየ ጊዜ በሁለቱ መካከል ተደረጉ የሚባሉ አሰቃቂ ወንጀሎችንም ሚቀንስ እንደሆነ አስረድተዋል።
ደንቡ አለማቀፍ ስምምነቶችንና የሌሎች ሀገራት ተሞክሮዎችን በመዉሰድ የስራ ስዓት፣ የእረፍት ጊዜና ሌሎች መብቶች እንዲካተቱበት ሆኖ እየተዘጋጅ ነው ያሉት ሀላፊዉ ነገር ግን የቤት ሰራተኛነት ከቤት ዉስጥ ሆኖ የሚሰራ ስራ እንደመሆኑ መጠን ከሌሎች የስረ ዘርፎች ስለሚለይ የቀጣሪንና የሰራተኛን ጥብቅ ተግባቦት እንደሚጠይቅ አመላክተዋል።

ደንቡ ብዙ ጥናት ተደርጎበታል፣ ብዙ የሚመለከታቸዉ ተቋማትም ተሳትፈዉበታል የተባለ ሲሆን ከዚህ ጎን ለጎንም በቴከኖሎጅ የታገዘ ሆኖ ህገ-ወጥ ደላሎችን ከአሰራሩ በማስወጣት አሰሪና ተቀጣሪን በቀጥታ የሚያገናኝ እንዲሆን ታሰቦ እየተዘጋጀ እንደ ሆነም አቶ ጥዑመዝጊ በርሔ ጠቁመዋል።
አቶ ጥዑመዝጊ በርሔ ሰራተኛውም ሆነ አሰሪው በአቅራቢያቸው በሚገኝ ወረዳ በመቅረብ "የሰራተኛ መታወቂያ" ወይም Labor ID በማዉጣት ቀጣሪዉም እንዲሁ የአሰሪ መታወቂያ እንዲያወጡ በማድረግቀጥታ ሰራተኛ ከተቀጣሪ ጋር ያለምንም አማላጅ ተገናኝተው በዋጋና በስራ ሁኔታዎች ላይ ተስማምተዉ ውላቸውን በየወረዳው በሚገኘው የስራና ክህሎት ተወካይ አማካኝነት በህጋዊ መንገድ እንዲመዘገቡ የሚያግዝ ዘዴ እየተበጀ ነዉ ብለዋል ።
ለመጀመሪያ ጊዜ እየተዘጋጀ ነዉ በተባለዉ የቤት ሰራተኞች ደንብ ሁለቱም ወገን ተጠቃሚ ይሆኑበታል ተብሏል።
በፍትሐቤር ህግ ተጠቅሶ የሚገኘዉ አሽክርና ገረድ የሚለዉ ስያሜም ተገቢና ተስማሚ አይደል በሚል በዚህ ደንብ የግል አገልግሎት ቅጥር በሚል እንዲተካ ስለመደረጉም ሰምተናል።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…..
ገዛ ጌታሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments