በምክክሩ ሂደት የሚታዩ ክፍተቶች ከስር ከስር መፍትሄ እንዲሰጣቸው የሃገራዊ ምክክር ተሳታፊዎች ጠየቁ።
- 19 hours ago
- 1 min read
ሐምሌ 17 2018
በምክክሩ ሂደት የሚታዩ ክፍተቶች ከስር ከስር መፍትሄ እንዲሰጣቸው የሃገራዊ ምክክር ተሳታፊዎች ጠየቁ።
ከገጠማቸው ችግር አንዱ የአስተርጓሚዎች እጥረት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
የቋንቋ ችግር ሃሳብን እንዳይገድብ በምክክሩ መሃል በተለያዩ ቋንቋዎች አስተርጓሚዎች የተመደቡ ቢሆንም ከቡድኖቹ ብዛት አንፃር በቂ አስተርጓሚ የለም፤ ኮሚሽኑ ለዚህ አፋጣኝ መፍትሄ ቢፈልግ ሲሉ ጠይቀዋል።
ከኦሮሚያ ክልል እንደመጡ የነገሩን አቶ ያዕቆብ በላይነህ ምክክሩ እንደርሳቸው አይነት አካል ጉዳተኞችን በሚገባ ማሳተፉ የሚያስመሰግነው ነው፤ነገር ግን እርሳቸው ባረፉበት የሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ በቂ የህክምና አገልግሎት የለም፤ከመናበብ ችግር የተነሳም አካል ጉዳተኞች 4ኛ ፎቅ ድረስ ወጥተው እየተሰበሰቡ ነው፤ እነዚህ ችግሮች ቢስተካከሉ መልካም ነው ብለዋል።
ከሰሞኑ የነበረውን የምክክር ሂደት አስመልክተው የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ በትላንትናው እለት በሰጡት መግለጫ ሂደቱ የተሳካ እንደሆነ ጠቅሰው፤ አንዳንድ ከባድ የጤና እክል ገጥሟቸው ቀዶ ጥገና የተደረገላቸው ተመካካሪዎችም ነበሩ፤ የህክምና፣ የደህንነትና የትራንስፖርት ቡድኖች ጥሩ አገልግሎት እየሰጡ ነው ነገር ግን እየገጠሙ ያሉ ችግሮችን ከስር ከስር እንፈታለን የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ከተጀመረ 9ኛ ቀኑን በያዘው የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎችን ያካተተ እንደመሆኑ ተመካካሪዎቹ አዲስ አበባ ከገቡበት ሃምሌ1 ጀምሮ የምግብ፣ የመኝታ፣ የትራንስፖርት፣ የጤና፣ የህፃናት እንክብካቤና ሌላ ሌላውም አገልግሎት በሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኩል እየቀረበ መሆኑ ይታወቃል።የውይይት ቡድኖቹ የሚያደርጉት የሃሳብ ልውውጥ በዛሬው እለትም ቀጥሏል ተብሏል።
የምክክሩን ሂደት በገለልተኝነት እየታዘቡ ካሉ ተቋማት የተወጣጡ 50 ታዛቢዎች እንዲህ አይነቱን የአልግሎትና ተደራሽነት ክፍተቶችን እየተከታተለ እንዲታረሙ ለኮሚሽኑ ያሉ ችግሮችን በተመለከተ ጥያቄ እንደሚያቀርቡ በሰጡት መግለጫ መናገራቸው ይታወቃል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ...
ምንታምር ፀጋው
_edited.jpg)
