top of page

በልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ ገብተው እንዲሰሩ የሚፈቀድላቸው ባንኮች የውጪ ምንዛሪ አገልግሎት የመስጠት ግዴታ እንዳለባቸው ተነገረ።

  • 1 hour ago
  • 1 min read

መጋቢት 9/2018


በልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ ገብተው እንዲሰሩ የሚፈቀድላቸው ባንኮች የውጪ ምንዛሪ አገልግሎት የመስጠት ግዴታ እንዳለባቸው ተነገረ።


የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ስራ ላይ መዋሉ ይታወቃል።


አዋጁ ከደነገጋቸው ግዴታዎች አንዱ በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ በሚቋቋም የአንድ መስኮት አገልግሎት ባንኮችም ገብተው አገልግሎት መስጠት አለባቸው የሚለው እንደሆነ ተጠቅሷል።


አሁን ላይ በኢትዮጵያ 32 ባንኮች እንዳሉ ያመለከተው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከእነዚህ መካከል ከ15 እስከ 20 የሚሆኑት በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ገብተው ለመስራት የሚያስችላቸውን ፍቃድ ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል ብሏል።


የዉጪ ባንኮችም ፍቃድ ይወስዳሉ ተብሎ እንደሚጠቅ ተናግሯል።



ከአዋጁ መወጣት በፊት በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች በዋናነት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንደሆነ ተጠቅሷል።


በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ገብተው ለመስራት ፍቃድ የሚወስዱ ባንኮች የውጭ ምንዛሪ አገልግሎት የመስጠት ግዴታ እንዳለባቸው ተነግሯል።


የባንክ አገልግሎት መስጠት የሚችሉት ግን በዚያው በልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ ላሉ የማህበረሰብ አባላት ብቻ ነው ተብሏል።


በአንድ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚሰሩ ባንኮችን ቁጥር ብሄራዊ ባንክ ሊወስን እንደሚችልም ተጠቅሷል።


ባንኮቹ ቅርንጫፍ መክፈት ይችላሉ የተባለ ሲሆን ንዑስ ቅርንጫፍ ግን መክፈት እንደማይፈቀድላቸው ተመልክቷል፡፡


ብሄራዊ ባንክ በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ለሚሰሩ የፋይናንስ ተቋማት ባወጣው መመሪያ ዙሪያ በስካይ ላይት ሆቴል ውይይት እየተካሄደ ነው።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..


ንጋቱ ረጋሳ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page