top of page

በህብረት ስራ ማህበራት ላይ በተሰራው የሪፎርም ስራ የተለያዩ ችግሮች መለየታቸው ተነገረ።

  • Apr 21
  • 1 min read

ሚያዝያ 13/ 2018

በህብረት ስራ ማህበራት ላይ በተሰራው የሪፎርም ስራ የተለያዩ ችግሮች መለየታቸው ተነገረ።


በሪፎርም ስራው 31,299 የህብረት ስራ ማህበራት አድርሻ የሌላቸው እና በስም ብቻ የሚታወቁ ሆነው ተገኝተዋል ተብሏል።


5,000 የህብረት ስራ ማህበራት ደግሞ ራሳቸውን ችለው መቀጠል የማይችሉ እንደሆኑ መረጋገጡ ተነግሯል።


እነዚህ ማህበራት ተዋህደው ህልውናቸውን እንዲያስቀጥሉ መደረጉን ሰምተናል።


የሪፎርም ስራው ከመጀመሩ በፊት በአገር አቀፍ ደረጃ 125,453 አሉ በሚል ሪፖርት ሲደረግ እንደቆየ ሠምተናል።


በስም ብቻ ከሚታወቁትና ራሳቸውን ችለው መቀጠል አልቻሉም ከተባሉት ውጪ ያሉት በቁጥር 89,453 ሆነው እንደተገኙ ተጠቅሷል።

ከእነዚህም መካከል 66 በመቶዎቹ በርካታ ችግሮች ያሉባቸው እንደሆኑ ሪፎርሙ አሳይቷል ተብሏል።


የህብረት ስራ ማህበራት ችግሮች ተለይተው እንዲፈቱ ከማድረግ ባሻገር ወደ ማህበረሰቡ ቀርበው አገልግሎት እንዲሰጡ ትኩረት መሰጠቱን የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌትነት ታደሠ ተናግረዋል።


ለዚሁ ሲባል 3,200 የቀበሌ የህብረት ስራ ማህበራት አደራጆች ለ10 ቀናት የቆየ ስልጠና ወስደው ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል።


ዛሬ ደግሞ 4,000 የሁለተኛው ዙር ሰልጣኞች በ6 ማዕከላት ስልጠና መከታተል መጀመራቸውን ዛሬ ይህንኑ አስመልክቶ በአዳማ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀ ስነ ስርዓት ላይ ተናግረዋል።


አሁን ላይ በኢትዮጵያ ያሉ የህብረት ስራ ማህበራት ከ56 ቢሊየን ብር እስከ 60 ቢሊየን ብር ካፒታል ያንቀሳቅሳሉ ተብሏል።


26 ሚሊየን አባላት እንዳሏቸውም ተነግሯል።


ለጥቅል ሀገራዊ ምርት ወይም GDP የሚያበረክቱት ድርሻ ከ2.5 በመቶ በላይ እንደሆነ ሠምተናል።


ንጋቱ ረጋሣ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page