top of page

በ"ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ዓቃቢ ህግ ክስ እንዲመሰርት 7 ቀናት ተፈቀደለት፡፡

  • 6 minutes ago
  • 1 min read

ሚያዝያ 21/2018

በ"ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ዓቃቢ ህግ ክስ እንዲመሰርት 7 ቀናት ተፈቀደለት፡፡


በፊንቴክ ኢንቨስትመንትሽፋን በተፈጸመ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮችን ጉዳይ ለመመልከት የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዛሬ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለ ዓቃቢ ህግ ክስ መመስረቻ 7 ቀን የፈቀደው፡፡


ፍርድ ቤቱ ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው ፖሊስ የምርመራ ስራዎችን አጠናቆ አንዲያቀርብ ነበር፡፡


በዛሬው ችሎትም ፖሊስ ምርመራውን መጨረሱንና ጉዳዩን ለዓቃቢ ህግ ማስተላለፉን አስረድቷል፡፡


ዓቃቢ ህግም ክስ ለመመስራት ፍርድ ቤቱን 10 ቀናት ጥይቆ 7 ቀናት ተፈቅዶለታል፡፡


በዚህም ለሚያዚያ 28/2018 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡


የፊንቴክ ኢንቨስትመንት ድርጅትን ባልተገባና በተጋነነ መልኩ በማስተዋወቅ በህገወጥ መንገድ ከተሰበሰበው ገንዘብ ተጋሪ በመሆን የተጠረጠሩ ሰለሞን ቦጋለ፣ ሰራዊት ፍቅሬ፣ ዳንኤል ተገኝ፣ አብርሃም ግዛው፣ ይገረም ደጀኔ፣ መንሱር ጀማል እና ካሊድ ናስር የተባሉ ታዋቂ አርቲስቶችና የማስታወቂያ ባለሙያዎችንም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ካዋላቸው አንድ ወር ሆኗቸዋል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page