top of page

ስታንዳርድ ኢንሹራንስ አ.ማ፤ በኢትዮጵያ 19ኛው የመድህን ሰጪ በመሆን ከቀናት በኋላ ገበያውን ይቀላቀላል ተባለ።

  • sheger1021fm
  • Nov 25
  • 1 min read

ህዳር 16 2018


ስታንዳርድ ኢንሹራንስ አ.ማ፤ በኢትዮጵያ 19ኛው የመድህን ሰጪ በመሆን ከቀናት በኋላ ገበያውን ይቀላቀላል ተባለ።


ኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ሽፋን ካላደገባቸው እና በኢኮኖሚው ውስጥ ያለው ድርሻም ዝቅተኛ ከሆነባቸው ከቀዳሚ ሀገሮች ውስጥ መሆኗ ይነገራል።


''በኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ሽፋን ገና ያልደረሰባቸው ብዙ የስራ ዘርፎች አሉ'' ሲሉ የስታንዳርድ ኢንሹራንስ አ.ማ ዋና ሰራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን አሰፋ ነግረውናል።


ከ305 ሚሊየን ብር በላይ ካፒታል በማስመዝገብ ከብሔራዊ ባንክ እውቅና በማግኘት 19ኛው የኢንሹራንስ ሰጪ ኩባንያ በመሆን ስራ የሚጀምረው ስታንዳርድ ኢንሹራንስ፤ የአዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ስራ ማህበር 1747 አባላት የመሰረቱት መሆኑን ዋና ስራ አስፈፃሚው ነግረውናል።

ree

የኢንሹራንስ ተቋሙ ትልቁ ባለድርሻም አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ስራ ማህበር ነው ተብሏል።


በሳምንቱ መጨረሻም የኢንሹራንስ ተቋሙ እና የኅብረት ስራ ማህበሩ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።


ዋና ሰራ አስፈፃሚው አቶ ሰለሞን፣ ስምምነቱ አዋጭ ለሚሰጠው የብድር አገልግሎት ስታንዳርድ ኢንሹራንስ የመድህን ሽፋን ለመስጠት እንዲችል ለማድረግ በማሰብ የተፈረመ ነው ብለውናል።


ከሁለት ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ስራ ይጀምራል የተባለው ስታንዳርድ ኢንሹራንስ፣ የጠቅላላ (General) እና የህይወት(life) ኢንሹራንስ አገልግሎትን በመስጠት ስራውን ይጀምራል ተብሏል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…


ቴዎድሮስ ወርቁ

Recent Posts

See All
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

ታህሳስ 6 2018 በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page