ሰኔ 5 2017- ወደ እንግሊዝ ለንደን ለማምራት የተነሳ የህንድ የመንገዶች አውሮፕላን ተከሰከሰ
- sheger1021fm
- 2 days ago
- 1 min read


242 ሰዎችን ያሳፈረው አውሮፕላን የተከሰከሰው ከአህመድአባድ ኤርፖርት እንደተነሳ ወዲያውኑ እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡
አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት ስፍራ ከባድ ጭስ እየተትጎለጎለ ነው ተብሏል፡፡
የወደቀው አውሮፕላን ቦይንግ 787 ድሪም ላይነር መሆኑ ታውቋል፡፡
የእሳት አደጋ ተከላካዮች ቃጠሎው ለማጥፋት እየታገሉ ነው ተብሏል፡፡
ከአደጋው በሕይወት የተረፉ ሰዎች ስለመኖራቸው የተሰማ ነገር የለም፡፡
አደጋ የገጠመው አውሮፕላን የኤር ኢንዲያ አየር መንገድ ንብረት መሆኑ ታውቋል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Commentaires