''በሎጅስቲክስ ዘርፍ ያለውን የባለሞያዎች ክፍተት ለመሙላትም ባለሞያዎችን በማሰልጠኑ እበረታለሁ'' የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር
- sheger1021fm
- 14 minutes ago
- 1 min read
ታህሳስ 8/2018
በገቢና በወጪ ንግድ፣ በጉምሩክ፣ በወደብ እና በመሰል ዘርፎች የባለሞያዎች እጥረት ስላለ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በትምህርት ስርዓታቸው አካትተው ሊሰሩበት ይገባል ተብሏል፡፡
በሎጅስቲክስ ዘርፍ ያለውን ይህንን የባለሞያዎች ክፍተት ለመሙላትም ባለሞያዎችን በማሰልጠኑ እበረታለሁ ሲል የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡

በተለይም በዘርፉ ሴቶች በበቂ እንዲሰማሩ እየተሰራ ነው የተባለ ሲሆን፤ በዲግሪ ተመርቀው በየክልሉ ስራ ሌላቸው ሴቶች ተመልምለው ወደዚህ ዘርፍ የሚያስገባቸውን ስልጠና እየተሰጣቸው መሆኑ ተነግሯል፡፡
በክልሎች በኩል ተመልምለው በአዲስ አበባ በዲፕሎማ ደረጃ ሲሰለጥኑ የቆዩ 94 ሴቶችም በትናንትናው ዕለት ተመርቀዋል፡፡

በምረቃ መርሀግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር) ተመራቂዎቹን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ወደ ስራ እንዲገቡ ይደረጋል ብለዋል፡፡
ሴት ተመራቂዎቹን በማሰልጠን እንደ አንድ ባለድርሻ እየሰራ የነበረው የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር ፍራኦል ጣፋ በሎጀስቲክስ ዘርፍ የባለሙያዎች እጥረት መኖሩን ተቅሰው ከሚሰጡት አጫጨር ስልጠናዎች በተጨማሪ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በትምህርት ስርዓታቸው ዉስጥ አካትተው ባለሞያችን በማፍራቱ ሊሰሩበት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ከየክልሉ ተመልምለው በዲፕሎማ የተመረቁት ሴቶች ምን ምን ላይ ነው የሰለጠኑት ስንል የጠየቅናቸው፤ በኢትየጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የኢትዮጵያ ትሬድ ሎጅስቲክስ ፕሮጀክት ማናጀር አቶ ደሳለኝ ጌታሁን ሰልጣኞቹ፣ በገቢና በወጪ ንግድ፣ በጉምሩክ፣ በወደብ እና በመሰል ዘርፎች እንደሰለጠኑ ነግረውናል፡፡

አሁን ላይ በዘርፉ የተሰማሩት ባለሞያች የወንዶች ቁጥር ክፍ ያለ በመሆኑና ሴቶችም ወደ ዘርፉ ለማስገባት በአሁን ዙር ሴቶች ብቻ ተመርጠው እንዲሰለጥኑ መደረጉንም አንስተዋል አቶ ደሳለኝ፡፡
በሎጀስቲክስ ዘንድ የሚሰለጥኑ ተመራቂዎች ወደ ስልጠና ሲገቡ ቢያንስ 40 ከመቶዎቹ ወዲያው ስራ እንዲያገኙ የማድረግ ስምምነት ከባለድርሻ አካላት እንደሚደረግ እና ከትናንት ተመራቂዎችም በዚሁ ስምምነት መሰረት ስራ ያገኙ እንዳሉ ተነግሯል፡፡
የተቀሩትም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ባጠረ ጊዜ ወደ ስራ እንዲገቡ ይደረጋል መባሉንም ሰምተናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
ማንያዘዋል ጌታሁን








