top of page

ሰኔ 30 2017 - የተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ

  • sheger1021fm
  • Jul 7
  • 1 min read

የኢትዮጵያ ግብርናን ከኬሚካል ማዳበሪያ ያላቅቃሉ የተባሉ የፈጠራ ሃሳቦች፤ በተለያዩ ጊዜያት ተሰሩ ተብሎ ሲነገሩ ሰምተናል፡፡


እነዚህ የተፈጥሮ ማዳበሪያዎች የአፈር አሲዳማነትን ከመከላከልም ባለፈ ምርትና ምርታማነትን እንደሚያሳድጉም ይነገራል፡፡


በቅርቡ በተደረገው አዩቴ አፍሪካ ቻሌንጅ ኢትዮጵያ 2025 የስራ ፈጠራ ውድድር ላይ ከቀረቡና ውድድሩ ላይ አሸናፊ ከሆኑ ስራዎች መካከል የተፈጥሮ #የአፈር_ማዳበሪያ ዋነኛው ነው፡፡


አማረ አዲስ የናኔክስ ሾልሽን መስራችና በተፈጥሮ አፈር ማዳበር የውድድሩ አንዱ አሸናፊ ነው፡፡


ኢትዮጵያ ውስጥ ቀደም ባለው ጊዜ ያለው ግብርና ስራ ይቀላጠፍ የነበረው በተፈጥሮ የአፈር ማዳበሪያ ነው፡፡


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በኬሚካል ማዳበሪያ ተቀይሯል ይላሉ፡፡


አሁን በቴክኖሎጂ በታገዘ መንገድ የተፈጥሮ ማዳበሪያን ማምረት እንችላለን ይህም በሙከራ አረጋግጫለሁ በማለት ያስረዳሉ፡፡

ree

ሌላው የውድድሩ አሸናፊ ዶክተር ባምላክ ካሳሁን ተፈጥሯዊ የአፈር ማዳበር የእስሳት መኖና ለባዮ ጋዝ የሚያገለግል የፈጠራ ስራን ሰርተዋል፡፡


ምርቱም ሙከራ ተደርጎለት ውጤታማ መሆኑን አይተናል ሲሉ ያስረዳሉ፡፡


አቶ አማረ አዲስ አሁን የኬሚካል ማዳበሪያ ዋጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል ይህ ደግሞ በምርቶች ዋጋ ጭማሪ እንዲኖር እያደረገ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡


የኬሚካል ማዳበሪን ለማስቀረት በማሰብ የአፈር ማዳበሪያ የፈጠራ ስራ የሰሩት ሁለቱም ባለሙያዎች ፋይናንስ ችግር ከተቀረፈልንና የምናለማበት ቦታ መንግስት ካመቻቸልን ምርታችንን በፍጥነት ለገበሬው አምርቶ ለማቅረብ እኛ ተዘጋጅተናል በማለት ነግረውናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…


በረከት አካሉ

Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page