ሰኔ 30 2017 - የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ላይ እየተደረገ ያለው ማሻሻያ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶችን ወደ ቀድሞው ማነቆ ሊመልሳቸው ነው የሚል ስጋት ፈጥሯል
- sheger1021fm
- Jul 7
- 1 min read
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ በስድስት ዓመት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ተሻሽሏል፡፡
ቀድሞ የነበረው ህግ ከሚያገኙት የገንዘብ ድጋፍ ከ10 በመቶ በላይ ከሃገርና ከውጭ ካሉ የገንዘብ ምንጮች የሚያገኙ ከሆነ በፖለቲካና መብት ጉዳይ ላይ እንዳይሰሩ ይከለክል ነበር፡፡
የተጠቀሰው እና ሌሎችም የሲቪል ማህበራትን አላሰራ ያሉ አንቀፆች ተሻሽለው ከ6 ዓመት በፊት አዋጁ ፀድቆ ነበር፡፡
አሁን በአዋጁ ላይ እንደገና እየተደረገ ያለው ማሻሻያ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶችን ወደ ቀድሞው ማነቆ ሊመልሳቸው ነው የሚል ስጋት ፈጥሯል፡፡
አዲሱ የህግ ማሻሻያ በምርጫ ጉዳይ ማህበረሰብን ለማንቃትና መሰል ስራዎች ለመስራት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከናካቴው ከውጭ ገንዘብ መቀበል አይችሉም ይላል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. https://www.mixcloud.com/ShegerFM/586/
ንጋቱ ረጋሣ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il












Comments