ሰኔ 27 2017 - የአለም ባንክ ለኢትዮጵያ 1 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ እና ብድር ለመስጠት ተስማማ
- sheger1021fm
- Jul 4
- 1 min read
የአለም ባንክ የ1 ቢሊዮን የፋይናንስ ስምምነትን የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ እና የአለም ባንክ የኢትዮጵያ የኤርትራ፣ የሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ዳይሬክተር ማሪያም ሳሊም ፈርመውታል፡፡፡
በአንድ ቢሊዮን ዶላሩ ምን ያህሉ በድጋፍ እና ምን ያህሉ ደግሞ በረጅም ጊዜ የሚመለስ ብድር እንደሆነ በገንዘብ ሚኒስቴር መግለጫ ላይ አልተጠየቀም፡፡

ገንዘቡ የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አካታች እድገትን ለማገዝ ይውላል ተብሏል፡፡
የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት፣ የንግድ ተወዳዳሪነትን ለማበርታት፣ የሀገር ውስጥ የሀብት አሰባሰብን ለማጠናከር፣ ግልፅ እና ውጤታማ የመንግስት አስተዳደርን ለማሳደግ እንዲሁም ማህበራዊ አገልግሎቶችን በዘላቂነት ማረጋገጥ በአንድ ቢሊዮን ዶላር የሚሰሩ ስራዎች መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡
ስምምነቱ የአለም ባንክ የኢትዮጵያ የሪፎርም አጀንዳ ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል የተባለ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት የአለም ባንክ ማመስገኑ በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il












Comments