ሰኔ 18 2017 - በአዲስ አበባ የነዳጅ ምርት በመደበቅ እጥረት እንዲፈጠር አድርገዋል የተባሉ 3 የነዳጅ ማደያዎች ታሽገዋል፤ ሰራተኞቹም በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰማ
- sheger1021fm
- Jun 26
- 1 min read
በአዲስ አበባ የነዳጅ ምርት በመደበቅ እጥረት እንዲፈጠር አድርገዋል የተባሉ 3 የነዳጅ ማደያዎች ታሽገዋል፤ ሰራተኞቹም በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰማ፡፡
በከተማዋ በቂ የነዳጅ አቅርቦት አለም ተብሏል፡፡
በአዲስ አበባ የሚከወነውን የነዳጅ ግብይት የሚቆጣጠረውን የከተማዋን ንግድ ቢሮ ከሰሞኑ በከተማዋ የሚስተዋለው ረጃጅም የነዳጅ ሰልፍ ከምን የመጣ ነው ስንል ጠይቀነዋል፡፡
የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አሸናፊ ብርሃኑ እርግጥ ነው ከሰሞኑ ባደረግነው ክትትል ናፍጣ ለመቅዳት የሚደረጉ ረጃጅም ሰልፎች ነበሩ ይህ የተፈጠረው እጥረት ኖሮ ሳይሆን ጥቂት ማደያዎች ዋጋ ሊጨምር ይችላል በሚል የነዳጅ ምርት በመደበቅ እጥረት እንዲፈጠር በማድረጋቸው ነው ብለዋል፡፡

በተለይም ባለፉት የቅዳሜና እሁድ ቀናት በርከት ያለ መጠን ያለው የነዳጅ ምርት ሸሽገው ተገኝተዋል የተባሉት ማደያዎች ተዘግተዋል ባለቤቶቹና ሰራተኞቹ በቁጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ እየታየ ነው ያሉን ሃላፊው የትኞቹ ማደያዎች እንደሆኑም በዝርዝር አስረድተዋል፡፡
በከተማዋ ያሉ 125 ማደያዎች ምን ያህል ነዳጅ ይዘዋል፤ግብይቱንስ እንዴት እየከወኑት ነው የሚለውን በቀን በቀን 3 ጊዜ እንደሚቆጣጠሩ የነገሩን አቶ አሸናፊ በአሁኑ ወቅት ከተማዋ የሚያስፈልጋት ያህል የነዳጅ ምርት አለ፤የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየውም ከ6 ሚሊዮን ሊትር በላይ ነዳጅ አለ፤በሁሉም ማደያዎች የነበሩት ሰልፎች እየቀነሱ ግብይቱ የተረጋጋ ሆኗል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ነዳጅ የሚጭኑ ቦቴዎችን በተመለከተ የተቀመጠው ስታንዳርድ እደሚያሳየው ነዳጅ የጫነ ቦቴ ከጂቡቲ ተነስቶ በ3 ቀናት ውስጥ አዲስ አበባ መድረስ ይኖርበታል፡፡
ይሁንና የተለያዩ ምክንያችን በመጥቀስ መንገድ ላይ ሆን ብለው የሚዘገዩ ቦቴዎችም ሰው ሰራሽ እጥረት እየፈጠሩ ነው፤ በዚህ በኩል በተሰራው የቁጥጥር ስራ ባለፈው እሁድ ብቻ መንገድ ላይ የቆዩ 16 ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች ወደ አዲስ አበባ ገብተው እንዲያራግፉ በመደረጉ የነበረው እጥረት ተቀርፏል ብለውናል፡፡
በንግድ አዋጁ መሰረት ምርቶችን የመደበቅ ወንጀል ከ300,000 እስከ 500,000 ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና የማደያ ባለቤቱን ከ2 ዓመት እስከ 3 ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት እንደሚያስቀጣ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
ምንታምር ፀጋው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il












If you want an experience that can be described as mind-blowing, contact the Escorts in Aerocity! Our hot beautifulness is trained to deliver the best companionship, and the best intimate experiences!