ሰኔ 12 2017 - በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት ከ10,000 በላይ ሴቶች ያስገድዶ መደፈር ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ጥናቶች ያሳያሉ
- sheger1021fm
- 9 minutes ago
- 1 min read
በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት ከ10,000 በላይ ሴቶች ያስገድዶ መደፈር ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ጥናቶች ያሳያሉ፡፡
ይህ ችግርም ጠባሳ ጥሎ እንዳያልፍ ሊከወኑ ስለሚገቡ ጉዳዮች ባለሞያዎች መክረዋል፡፡
በክልሉ ሰላም ቢሰፍንም በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች ግን አሁንም ድረስ መቀጠላቸው ደግሞ ችግሩን ያባብሰዋል ተብሏል፡፡
በክልሉ ያለው የፈትህ ሥርዓት ወደ ነበረበት አለመመለሱ፣ የጤና ተቋማት ሙሉ በሙሉ ስራቸውን መከወን ባለመጀመራቸው እና በሌሎችም ችግሮች ምክንያት የሴቶች ጥቃት ሊቀጥል መቻሉን ጥናቶችን ጠቅሰው የነገሩን በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መምህርና የማህበረሰብ ሳይንስ አጥኝ የሆኑት አቶ ዘርዓብሩክ ዘውዱ ናቸው፡፡
የተለያዩ መሠረተ ልማቶች ወደ ስራ አለመግባታቸው ሴቶቹ ጥቃት ሲደርስባቸው ወዴት ሄደው አቤት ማለት እንዳለባቸው ይቸገራሉ የተባለ ሲሆን መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችም ቢሆኑ ተደራሽነታቸው ውስን ነው ተብሏል፡፡
ሙሉ ዘገባውን በድምጽ ያድምጡ…. https://www.mixcloud.com/ShegerFM/fyujye5656756/
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Comments