ራሚስ ባንክ ጠቅላላ ሀብቱ ከ4.2 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ተናገረ።
- sheger1021fm
- 11 minutes ago
- 1 min read
ህዳር 29 2018
ራሚስ ባንክ ጠቅላላ ሀብቱ ከ4.2 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ተናገረ።
ይህም በአንድ ዓመት ውስጥ የ85 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል ሲል ባንኩ ትናንት ባካሄደው ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ባወጣው ሪፖርት ተናግሯል።
ራሚስ ባንክ በበጀት ዓመቱ ከ400 ሚሊየን ብር በላይ ጠቅላላ ገቢ በማስመዝገብ ወደ ትርፍ ተሸጋግሬያለሁም ብሏል።
ገቢው በዓመቱ ውስጥ የ3,726 ከመቶ እድገት አሳይቷል ተብሏል።

ራሚስ ባንክ በ2017 በጀት ዓመት ከ20 ሚሊዮን ዶላር በላይ መሰብሰቡንም ጠቅሷል።
የቅርንጫፎቹን ብዛት 47፣ የደንበኞቹ ብዛት ደግሞ 352,000 መድረሳቸው በሪፖርቱ ላይ ሰፍሯል።
ባንኩ በበጀት ዓመቱ ማገባደጃ ላይ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያንና የካርድ ባንኪንግ አገልግሎቶቹን ለደንበኞቹ ማስተዋወቁን እና የላቁ የዲጅታል ባንክ አማራጮችን እንደ ኢንተርኔት ባንኪንግ፣ ዋሌት እና ኢ–ሙራባሃ የዲጀታል አገልግሎቶችን ለመተግበር እየሰራ መሆኑን አስረድቷል።
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🟦Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1












Comments