ምርትና አገልግሎት ያላቸውን፣ ሸማቹንና አሻሻጭን የሚያገናኝ የሞባይል መተግበሪያ በይፉ ስራ መጀመሩ ተነገረ።
- sheger1021fm
- 22 minutes ago
- 1 min read
ታህሳስ 18/2018
ምርትና አገልግሎት ያላቸውን፣ ሸማቹንና አሻሻጭን የሚያገናኝ የሞባይል መተግበሪያ በይፉ ስራ መጀመሩ ተነገረ።
መተግበሪያው "ዳንቴል" ይባላል።

በዳንቴል ሶፍትዌር የተዘጋጀው "ዳንቴል" የሞባይል መተግበሪያ አምራቾች ምርታቸውን፣ አገልገሎት አቅራቢዎች ያላቸውን አገልግሎት ሙሉ መረጃ የሚያስቀምጡበት፣ መረጃውን ደግሞ በየራሳቸው የማህበራዊ ትስስር ገፆች የሚያጋሩና ሽያጭ እንዲከናወን የሚያደረጉ ደግሞ የኮሚሽን ክፍያ እንዲያገኙ የሚያስችል ስርዓት ይዞ የመጣ ነው።
ይህም ለሸማቹ ገበያ ወጥቼ የት ምን አገኛለሁ የሚለውን የሚያቀልል፣ ለአምራቹም ሰፊ የገበያ እድል የሚፈጥር፣ በተለይ በሽያጭ ስራ ገቢ ለማግኘት ለሚፈልጉ ስልካቸውን ተጠቅመው ገቢ እንዲያገኙ የሚያስች እንደሆነ የድርጅቱ ሀላፊዎች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።
መተግበሪያው በሰው ሰራሽ አስተውህሎት(AI) ታግዞ ተጠቃሚዎችን ያማክራል ተብሏል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
ፍቅሩ አምባቸው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1








