top of page

መስከረም 8 2018 -መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።

  • sheger1021fm
  • 30 minutes ago
  • 1 min read

ይህን ያለው የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ነው።


ኢንስቲትዩቱ በበጋው የአየር ሁኔታ በሚኖር ወቅቱን ያልጠበቀ #ዝናብ በትግራይ፣ አማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ብሏል፡፡


ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት አከባቢዎች የዝናብ መቆራረጥ ሊኖር እንደሚችልም ተጠቁሟል።


ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት እንደ ቦረናና ጉጂ ዞኖች፣ ሲዳማ እና ደቡብ ኢትዮጵያ መደበኛ ዝናብ የሚኖራቸው መሆኑን ኢንስቲትዩቱ ተናግሯል።


የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍል ደግሞ ከመደበኛ በታች የሆነ የዝናብ መጠንና ስርጭት እንደሚያገኙ ተጠቁሟል።

ree

በሌላ በኩል የምዕራብና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንደሚያገኙም ተነግሯል።


ኢንስቲትዩቱ ግንቦት ላይ የሰጠው የክረምት ወቅት የአየር ጠባይ ትንበያ መሬት ላይ ከተከሰተው ጋር የተጣጣመ እንደነበረም ተነግሯል፡፡


ማህበረሰቡ የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ እንዲሰብሰቡ ማድረግ ከመደበኛ በታች ዝናብ በሚስተዋልባቸው የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍል የሚገኘውን የዝናብ መጠንና ስርጭት በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል ሲል ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል።


ፍቅሩ አምባቸው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page