top of page

መስከረም 29 2018 - ኢትዮጵያ ዛሬ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነትን በይፋ ትቀላቀላለች።

  • sheger1021fm
  • Oct 9
  • 1 min read

ዛሬ ከሰዓት በኋላ የተለያዩ ምርቶች በየብስ እና በአየር በይፋዊ ስነ ስርዓት ወደ ተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት እንደሚሸኙ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ነግሮናል

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንድሙ ፍላቴ ይህንኑ ነግረውናል።


በአየር ትራንስፖርት የስጋ፤ የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች ወደ ተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት እንደሚላኩ ተናግረዋል።


ይሄኛው የንግድ ልውውጥ በምስራቅና በደቡብ አፍሪካ ሀገራት ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተጠቅሷል።


በየብስ ትራንፖርት ደግሞ ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎች ወደ ኬንያ፣ ሶማሊያ እና ወደ ደቡብ አፍሪካ ይላካሉ ተብሏል፡፡


ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ለመተግበር ሰፋ ያለ ዝግጅት ስታደርግ እንደቆየች ተጠቅሷል።


የንግድ ሂደቱን ተግባራዊ ለማድረግ በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሚመራ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሲሰራ ቆይቷል ተብሏል።


ኮሚቴው የገንዘብ ሚኒስቴር ፤ የገቢዎች ሚኒስቴር ፤ የጉሙሩክ ኮሚሽን ፤ ብሄራዊ ባንክ ፤ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ፤ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ፤ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ፤ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና የግል ዘርፍ ተወካዮችን የያዘ መሆኑ ተነግሯል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….


ንጋቱ ረጋሳ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page