መስከረም 14 2018 - በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳት ከሚያስተናግዱ አህጉራት አፍሪካ ቀዳሚዋ ናት
- sheger1021fm
- Sep 24
- 1 min read

አህጉሪቱ ለአካባቢ ብክለት የምታበረክተው አስተዋፅኦ ግን ዝቅተኛ ነው ፡፡
በቅርቡ በተደረገው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ምክክር ከተደረጉባቸው ጉባኤዎች መካከል ለአየር ንብረት ለወጥ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ ማቅረብ የሚለው አንዱ ሲሆን አፍሪካ ከተደራዳሪነት ይልቅ መፍትሄ አቅራቢ እንድትሆን መስራት ይገባልም ተብሏል በጉባኤው፡፡
በዚህ ጉባኤ ከ200 ቢሊዮን ዶላር በላይ ፈንድ ቃልም ተገብቷል፡፡
የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአካባቢና የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነትና ስትራቴጂክ አጋርነት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ መንሱር ደሴ አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ችግሮች የራሷን መፍትሄ እስካሁንም ድረስ ስትወስድ ነበር ብለዋል፡፡
በቅርቡም ኢትዮጵያ ባስተናገደችው የአህጉሪቱ የአየር ንብረት ጉባኤ የተለያዩ አፍሪካዊ መፍትሄዎች መቅረባቸውን ይጠቅሳሉ፡፡
አፍሪካ አሁን እየሰራች ያለው ለአየር ንብረት ለውጥ ተፈጥሯዊ መፍትሄ መስጠት ላይ ነው አለም ደግሞ ለዚህ ትኩረት አልሰጠም ይላሉ፡፡
አፍሪካ ውስጥ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ የሚሆን ማዕድን አለ ኢትዮጵያ ባካሄደችው የአህጉሪቱ የአየር ንብረት ጉባኤ እነዚህ ማዕድናት እዚሁ አፍሪካ ውስጥ ወደ ስራ መዋል የሚቻልበት ዙሪያም ምክክር ተደርጓል በማለት አቶ መንሱር ደሴ ያስረዳሉ፡፡
አለም ላይ ያለው የአየር ንብረት የፋይናንስ አካሄድ ትክክል አይደለም የሚሉት አቶ መንሱር ደሴ ይህም መስተካከል አለበት ሲሉ ይናገራሉ፡፡
በዚህ ዙሪያ የሚሰሩ እረጂ ተቋማትም ይሁን ሀገራት ከአፍሪካ ጋር አጋር በመሆን አብረው መስራት አለባቸው ይህ ከሆነ በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ የሚታይ መፍትሄ ማምጣት ይቻላል ባይ ናቸው፡፡
አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚደርስባት የጎርፍ ፣ ድርቅ ፣ ረሃብ እና ሌሎች ችግሮች እንዲያበቁ በትኩረት መስራት አለባት ተብሏል፡፡
በረከት አካሉ
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…👇👇👇👇👇👇












Comments