top of page

ሐምሌ 3፣ 2016 የሸጎሌ የቁም እንስሳት ገበያ ከቦታው አንዲነሳ በፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ ተሰጠ፡፡

  • Jul 10, 2024
  • 1 min read

የሸጎሌ የቁም እንስሳት ገበያ ከቦታው አንዲነሳ በፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ ተሰጠ፡፡


በመኖሪያ መንደር አካባቢ የተገነባውና በሚፈጥረው የአካባቢ ብክለት ነዋሪዎች ሲያማርሩበት የቆየው የገበያ ማዕከሉ ከዚህ ቀደምም ከቦታው እንዲነሳ በተከማዋ #ፍርድ_ቤት ጉለሌ ምድብ ችሎት ተወስኖበት ነበር፡፡፡


ተከሳሾች የጉለሌ ክፍለ ከተማ ንግድ ፅ/ቤት እና የኢትዮጵያ የቁም እንስሳት ነጋዴዎች ማህበር ይግባኝ ብለው ሲከራከሩ ቆይተዋል፡፡

የአካባቢውን ህዝብ ወክሎ ቁም ለአካባቢ የተሰኘው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅትም ለአምስት ዓመት በፍርድ ቤት ሞግቶ የመጨረሻ ውሳኔ ከትናንት በስትያ ተሰጥቷል፡፡


ገበያው #የአካባቢ_ብክለት ስለመፍጠር አለመፍጠሩ በገለልተኝነት ማስረጃ እንዲያቀርብ የተጠየቀው የፌዴራሉ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ብክለት ስለመኖሩ በማረጋገጡ ፍርድ ቤቱ ገበያው ከቦታው እንዲነሳ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page