top of page

ሐምሌ 28 2017 - የተቀማጭ ገንዘብ መድህን ፈንድ በተቀመጠው መሰረት የቆጣቢዎችን ገንዘብ መመልስ ችሎ ይሆን?

  • sheger1021fm
  • Aug 4
  • 1 min read

ባንኮችና የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት በተለያየ ምክንያት ከስረው ከገበያ ቢወጡ፣ ለቆጣቢዎች ዋስትና እሰጣለሁ፣ በፋይናንስ ተቋሙ ያስቀመጡትን ገንዘብ እመልስላቸዋለው ብሎ ስራ የጀመረው የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድህን ፈንድ በተቋቋመ በአጭር ጊዜ ውስጥ በተግባር ተፈትኗል።


በመድህን ፈንዱ አሰራር መሰረት የፋይናንስ ተቋም ከስሮ ቢዘጋ ከ100,000 ብር በታች ተቀማጭ ያላቸው የባንክ ደንበኞች ሙሉ ገንዘባቸውን ከ90 ቀን ባነሰ ጊዜ ሙሉ ለሙሉ ያገኛሉ።


በቅርብ ጊዜ ውስጥ አንድ ማይክሮ ፍይናንስ ተቋም ከስሮ ከገበያ ስለመውጣቱ ተሰምቷል፡፡


በመጠንና አቅሙ አነስተኛ ነው የተባለው የማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ውስጥ የቁጠባ ሂሳብ ያላቸው ሰዎች ብዙ አለመሆናቸው ቢነገርም አዲስ ለተቋቋመው የመድህን ፈንድ ግን አጋጣሚው በተግባር የሚፈተንበት ሆኗል።


በአሰራሩ በተቀመጠው መሰረት የቆጣቢዎችን ገንዘብ መመልስ ችሎ ይሆን? ይህን ለማድረግስ ምን ያህል ጊዜ ይወስድበታል?


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ……


ቴዎድሮስ ወርቁ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page