top of page

ሐምሌ 25 2017 - አቤቱታ የቀረበበትን የምክር ቤት ወንበር ድልድልን የተመለከተውን ህግ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማፅደቁ ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Aug 1
  • 1 min read

ከዚህ ቀደም ለህገ መንግስት አጣሪ ጉባኤ አቤቱታ የቀረበበትን የምክር ቤት ወንበር ድልድልን የተመለከተውን ህግ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማፅደቁ ተነገረ፡፡


ያለ አዋጅ ማሻሻያ ተደርጎበት የጸደቀው የክልሉ ምክር ቤት የወንበር ቁጥር ቀድሞ ከነበረበት 99 ወደ 165 ያደገው መቀመጫ እንደ አዲስ የሚዋቀረውን ለተቀሩት የምርጫ ክልሎች የሚከፋፈል ነው ተብሏል፡፡


ክልሉ ከዚህ ቀደም በአዋጅ ያፀደቀውን የምርጫ ክልል አወቃቀር የሚያስቀረውን ይህንን ውሳኔ ያሳለፈው የአዋጅ ማሻሻያ ሳያደርግ ቃል በቀረበ ገለፃ ላይ ተመስርቶ ነበርም ተብሏል፡፡


የክልሉ ምክር ቤት የመቀመጫ ቁጥሩን ለማሳደግ ያቀረበውን ማሻሻያ ተከትሎ የቦሮ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባላት በወቅቱ ሀሳቡን በመቃወማቸው ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ ለእስር መደረጋቸውን ፓርቲው መናገሩ ይታወሳል፡፡


ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አቤቱታ ያቀረበበትን የምርጫ ክልሎችን በአዲስ መልክ ለማዋቀር የአዋጅ ማሻሻያ ተደረገበትን ውሳኔ ተከትሎ የቦሮ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምን ይላል? የሚለውን ሀሳብ ለመቀበል የፓርቲው ፕሬዝዳንት ጋር ደጋግመን ብንደውል ልናገኛቸው አልቻልንም፡፡


ፓርቲው በወቅቱ በማሻሻያ ዙሪያ ያነሳው ቅሬታ እና ተቃውሞ በተለይም ውክልና ያገኘሁበትን የመተከል ዞን የመቀመጫ ቁጥርን ጥያቄ ውስጥ የሚጥልብኝ ነው በሚል መሆኑ ይታወሳል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… https://www.mixcloud.com/ShegerFM/653456/

የኔነህ ሲሳይ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page