top of page

ሐምሌ 25 2017 - ቡና ባንክ በማንኛውም አይነት ሞባይል ስልክ እንዲሁም ያለኢንተርኔትም የነዳጅ ክፍያ የሚከወንበት ስርዓት አስተዋወቀ

  • sheger1021fm
  • Aug 2
  • 1 min read

ቡና ባንክ በማንኛውም አይነት ሞባይል ስልክ እንዲሁም ያለኢንተርኔትም የነዳጅ ክፍያ የሚከወንበት ስርዓት አስተዋወቀ፡፡


ባንኩ የዲጂታል ክፍያ ስርዓቱን ያስጀመረው ከትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው ተብሏል፡፡


ቡና ባንክ ዛሬ በይፋ ያስተዋወቀው የክፍያ ስርዓት፤ በተለይ በነዳጅ ማደያዎች ውስጥ የሚስተዋሉ ረጃጅም ወረፋዎችን በመቀነሱ የራሱ የሆነ አስተዋጽዖ እንደሚያደርግም ተነግሮለታል፡፡

ree

የቡና ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ታፈሰወርቅ ንጉሴ፤ እስካሁን 12 ሚሊዮን ብር ገደማ በዚህ ስርዓት አገበያይተናል ብለዋል፡፡


የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ቡና ባንክን ተጠቅመዉ የነዳጅ ግዢን መፈጸም የሚችሉት፤ ከነዳጅ ማደያዉ *820# በመጠቀም ስልካቸዉ ላይ በሚደርሳቸዉ የማረጋገጫ መልዕክት፣ ‘’አቦል የሞባይል ባንኪንግ’’ መተግበሪያ ዉስጥ በመግባት ከውአር (QR) ኮድን ተጠቅሞ ስካን በማድረግ ወይም በነዳጅ ማደያው የቀረበውን የማጣቀሻ ቁጥር (Reference Number system) በመጠቀም መሆኑም ባንኩ አስረድቷል።

ree

ቡና ባንክ ከደም ብሎ የጀመረው እንዲሁም ዛሬ በይፋ ያስተዋወቀው ይህ ክፍያ የሚከወንበት ስርዓት፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የነዳጅ አቅርቦት ሰንሰለትን ግልፅነት እና ቅልጥፍና ለማሻሻል አንዱ አማራጭ እንደሆነም የተናገሩት፤ በትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የብሄራዊ የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ፕሮጀክት አስተባባሪ ሰልማን መሀመድ ናቸው፡፡


አሀን ላይ ባንኩ በተወሰኑ የተመረጡ የነዳጅ ማደያዎች የጀመረውን ይህን አገልግሎት በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች ለማስፋት አቅጃለሁም ብሏል፡፡


ቡና ባንክ ከተቋቋመ 15 ዓመታት ማስቆጠሩ፣ የባለአከሲዮኖቹ ብዛት 13,000 መሆናቸውን እንዲሁም የቅርንጫፎቹ ብዛት 456 መደረሱ ተነግሯል፡፡


ማንያዘዋል ጌታሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page