ሐምሌ 17 2017 - ኢትዮ ቴሌኮም ዘንድሮ 162 ቢሊየን ብር ገቢ አግኝቻለሁ አለ።
- sheger1021fm
- Jul 24
- 1 min read
በቴሌኮም ዘርፍ ደንበኛን ማቆየት በጣም ፈታኝ ነው ያሉት የኩባንያው ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በተለያዩ አገልግሎቶች ደንበኞቻችንን አቆይተናል ብለዋል።
በዚህም አጠቃላይ የደንበኞች ቁጥር 83.2 ሚሊየን ደርሷል ተብሏል፤ ይህም ከአምናው በ6.2 በመቶ ጨምሯል።
በኢትዮዽያ የመጀመርያው የ’ሞባይል መኒ’ አገልግሎት የሚሰጠው #ቴሌብር በ4 ዓመት ጉዞው ውስጥ በከፍተኛ ቁጥር ከደንበኞች እና ከሀገር ጋር ተላምዷል ተብሏል።
የቴሌ ብር ደንበኞች ቁጥር 54.8 መድረሱን ሰምተናል።
አገልግሎቱ ከተጀመረ ጊዜም አንስቶ 4.9 ትሪሊየን ብር ተገላብጧል ተብሏል።
በዚህ ዓመትም ቴሌ ብር 7 ሚሊየን ደንበኞችን በማፍራት 2.8 ትሪሊየን ብር ተላውሶበታል ተብሏል።
ቴሌ ብር አገልግሎት ከጀመረ አንስቶ 11.9 ሚሊየን ደንበኞች 25.8 ቢሊየን ብር መበደራቸውን ሰምተናል።
ይህ ቁጥር የዲጂታል ኢኮኖሚን ግንባታ የሚያስረዳ ነው ሲሉ ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል።
ተህቦ ንጉሴ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s











Comments